Tender Detail

Tender Details

  • Company Hibir Construction Corporation (ኅብር ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን)
  • Address ባህር ዳር ከተማ አማራ ፓይፕ ፋብሪካ ፊት ለፊት ዋና መ/ቤት ፡ አማራ ክልል ፡ ኢትዮጵያ, Phone: 058-320-35-76
  • Websitehttps://arwe.et/
  • Deadline07 Aug 2025, 12:00 AM
  • magazineአዲስ ዘመን
  • Bid Document Price200.00
  • opening date2025-08-07 00:00:00
  • Categories Construction Vehicle

ኅብር ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ለተለያዩ ፕሮጀክቶች አገልግሎት የሚውል ኤክስካቬተር ከነ ጃካመሩ በዘርፉ የተሰማሩ አቅራቢዎችን በግልጽ ጨረታ በማወዳዳር መግዛት ይፈልጋል።


 

የጨረታ ማስታወቂያ

 

ኮርፖሬሽናችን ለተለያዩ ፕሮጀክቶች አገልግሎት የሚውል ኤክስካቬተር ከነ ጃካመሩ በዘርፉ የተሰማሩ አቅራቢዎችን በግልጽ ጨረታ በማወዳዳር መግዛት ይፈልጋል። ስለሆነም ከዚህ በታች ኮርፖሬሽናችን ያስቀመጣቸውን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተወዳዳሪ ድርጅቶች በጨረታው መወዳዳር ይችላሉ።

 

.

የእቃው ዓይነት

መለያ

መለያ

ብዛት

ምርመራ

1

ሀይድሮሊክ ቸን ኤክስካቬተር

በጨረታ ሰነዱ ላይ ተያይዟል

ቁጥር

02

 

2

ጃካመር

በጨረታ ሰነዱ ላይ ተያይዟል

ቁጥር

02

 

 

  1. ተወዳዳሪዎች የዘመኑን ግብር ከፍለው የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የምዝገባ የምስ ወረቀት፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ እና TIN ሰርተፊኬት፣ እንዲሁም በጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችል የታ ሊራንስ ከገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን የተሰጠ ደብዳቤ እና ሌሎች ቴክኒካል ሰነዶችን ኮፒ (ቅጅ) እና ኦርጅናል (ዋና) በማለት ለየብቻ በፖስታ በማድረግ እንዲሁም የፋይናንሻል (የዋጋ) መሙያ ሰነዳቸውን ኮፒ (ቅጅ) እና ኦርጅናል (ዋና) በማለትና ለየብቻ እንዲሁም የጨረታ ማስከበሪያውን ለብቻ በማድረግ በአንድ በታሸገ ኢንቨሎፕ በማድረግ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 20 ተከታታይ ቀናት ውስጥ የመወዳዳሪያ ሰነዳቸውን ባህር ዳር ከተማ ከሚገኘው ዋና /ቤታችን የግዥ ዳይሬቶሬት ፍል በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
  2. ጨረታው 20ኛው ቀን ከቀኑ 900 ታሽጎ በዚሁ እለት 930 ይከፈታል። ይሁን እንጂ 20ኛው የመክፈቻ ቀን ከኮርፖሬሽናችን የሥራ ሰዓት ውጭ ከሆነ እና የመንግስት ካላንደር የሚዘጋው ከሆነ በቀጣዩ የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት የሚከፈት ይሆናል።
  3. የሚቀርበው የዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ ሕጋዊ የድርጅቱ ተወካይ ስም፣ ፊርማና ማህተም ይኖርባቸዋል።
  4. ተጫራቾች የሚሰጡት ዋጋ አዲስ አበባ የኮርፖሬሽናችን ማስተባበሪያ /ቤት ድረስ የማጓጓዝ እና ሌሎች ከእቃዎች ጋር የተያያዙ ማንኛውም ወጪዎች ተጫራቹ የሚሸፍን ይሆናል።
  5. በዚህ ጨረታ የሚሰጠው የመወዳደሪያ ዋጋ ጨረታው ከተከፈተበት ቀን ጀምሮ 60 (ስልሳ) ተከታታይ ቀናት የጸና ይሆናል።
  6. ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ የሚሆን ብር 500,000.00 (አምስት መቶ ሽህ ብር) የያዘ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ጋራንቲ በኮርፖሬሽናችን ስም ማለትም ኅብር ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን (Hibir Construction Corporation) በሚል የተሰራ እና ጨረታው ከሚከፈትበት ቀን ጀምሮ 90 (ዘጠና) ቀናት ጸንቶ የሚቆይ ማስያዝ አለባቸው።
  7. ተጫራቾች በጨረታው ማሸነፋቸው በደብዳቤ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ ባሉት 05 (አምስት) ተከታታይ ቀናት ውስጥ ያሸነፉበትን ጠቅላላ ዋጋ 10% በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ በኮርፖሬሽናችን ስም የተሰራ የባን ዋስትና (የውል ማስከበሪያ ዋስትና) ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
  8. ከአቅም በላይ የሆኑ ችግሮች ሲከሰቱ በሁለቱ ወገን /በሻጭ እና በገዥ የጋራ ውይይት ችግሩ ይፈታል። ጋራ ችግሮችን ለመፍታት ካልተቻለ በሚመለከተው ፍርድ ቤት ሁለቱም ወገን ቀርበው በሚወሰነው ውሳኔ የሚፈጠረው አለመግባባት ይፈታል፡፡
  9. ይህ የጨረታ ግዥ ሥርዓት እና መመሪያ የጨረታው የውል አካል ሆኖ ይወሰዳል።
  10. ጨረታው ከተከፈተ በኋላ ተጫራቶች ባቀረቡት የመወዳደሪያ ሃሳብ ላይ ለውጥ ወይም ማሻሻያ ማድረግና ከጨረታው ራሳቸውን ማግለል አይችሉም።
  11. በጨረታው ለተገለጸው ማሽን ዝርዝር የጨረታ ሰነድ ብር 200 (ሁለት መቶ ብር) በመከፈል ከኮርፖሬሽናችን ገንዘብ ያዥ ቢሮ ቁጥር 23 ቀርበው መግዛት ይችላሉ፡፡
  12. ጨረታውን ለማሸነፍ እንዲረዱት ለማንኛውም የኮርፖሬሽኑ ኃላፊ ወይም ሠራተኞች መደለያ የሰጠ ተጫራች አግባብ ባለው የወንጀለኛ መቅጫ ሕግ ድንጋጌ መሠረት መጠየቁ እንደጠበቀ ሆኖ ከጨረታው እንደሚሰረዝ አሸንፎ ውል ቢዋዋልም ውሉ ይሰረዛል።

 

ኅብር ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን

 

Save Tender