የኦሮሚያ ምርጥ ዘር ኢንተርፕራይዝ የCutsourcing Financial Report Preparation Service በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሠራት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር OSE/NCB/01/2018
የኦሮሚያ ምርጥ ዘር ኢንተርፕራይዝ የCutsourcing Financial Report Preparation Service በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሠራት ይፈልጋል።
ስለሆነም አስፈላጊውን መስፈርት የምታሟሉ በጨረታው መሳተፍ የሚትችሉ መሆኑን እየገለጽን ተጫራቾች፡
- የንግድ ምዝገባ ሰርትፍኬት
- የዘመኑን የታደሰ ንግድ ፈቃድ
- የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ ሰርተፊኬት
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (Tin No)
- የአቅራቢነት ማስረጃ (Suppliers List)
- የሚፈለግባቸውን የመንግሥት ግብር ስለመወጣታቸው የሚገልጽ ማስረጃ፣ ፎቶ ኮፒ ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር በማያያዝ ማቅረብ አለባቸው።
ተጫራቾች ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10 ተከታታይ ቀናት ሰነዱን በመግዛት በ10ኛው የሥራ ቀን ጨረታው የሚዘጋና የሚከፈት ይሆናል፡፡ የጨረታ ሰነድ መግዣ ዋጋ ብር 100 (አንድ መቶ) መሆኑን እየገለጽን፤ ተጫራቾች የዋጋ ማቅረቢያቸውን በፖስታ በማሸግ በተጠቀሱት ቀናት ከጠዋቱ 2፡30-8፡00 ሰዓት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ በማስገባት በጨረታው እንዲትሳተፉ እንጋብዛለን።
የጨረታ ሳጥኑ ከላይ በተጠቀሱት ቀናት 8፡00 ሰዓት ተዘግቶ በ8፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በኢንተርፕራይዙ ዋና ቤት ጎተራ አጎና ሠራዊት ሲኒማ አጠገብ ባለኬር ሕንፃ /Baleker Tower/ 4ኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው የኦሮሚያ ምርጥ ዘር ኢንተርፕራይዝ ቢሮ ቁጥር 402 ይከፈታል።
ኢንተርፕራይዙ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
የኢንተርፕራይዙ የሥራ ሰዓት፡
ከሰኞ-አርብ ጥዋት ከ2፡30-6፡30 ከሰዓት በኋላ ከ7፡30 11፡30 ነው።
ለበለጠ ማብራሪያ፡
ስ.ቁ 011-416 03 09/011-466-25-27 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል።
የኦሮሚያ ምርጥ ዘር ኢንተርፕራይዝ
