የሀላባ ዞን የዌራ ወረዳ ፋይ/ጽ/ቤት ለሴ/መ/ቤቶች አገልግሎት የሚውል ዕቃዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ
የሀላባ ዞን የዌራ ወረዳ ፋይ/ጽ/ቤት ለሴ/መ/ቤቶች አገልግሎት የሚውል ዕቃዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
1/ የጽ/መሣሪያ እና ሌሎች አላቂ የጽዳት ዕቃዎች (ሎት-1)
2/ ሞተር ሣይክል (ሎት-2)
3/ ኤሌትሮኒክስ (ሎት 3)
4/ ፈርኒቸር (ሎት 4)
በዚህ መሠረት፡-
- በዘርፉ የተሰማራችሁ ዘመኑ የታደሰ ንግድ ፍቃድ ማቅረብ የምትችሉ
- አቅራቢነት እና የግብር ከፋይነት ምስክር ወረቀት ያላቸው
- የቫት ተመዝጋቢነት ምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች ለእያአንዳንዱ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 100 (አንድ መቶ) በመክፈል ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባለው ተከታታይ 20 ቀናት ዘወትር በስራ ሰዓት ቢሮ ቁጥር 2 መግዛት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ለእያንዳንዱ 5000 (አምስት ሺህ ብር) በባንክ የተረጋገጠ COP ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳቸውን እያንዳንዱን አንድ ኦርጅናል አንድ ኮፒ በማዘጋጀት በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 21 ቀናት ውስጥ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ቢሮ ቁጥር 02 ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው በ21 አንደኛው ቀን ሰዓት 4፡00 ሰዓት ታሽጎ 5፡00 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ በዕለቱ ተጫራቾች ያለመገኘታቸው ጽ/ቤቱን ጨረታውን ከመክፈት የሚያግደው ነገር አይኖርም፡፡
- የጨረታው መክፈቻ ቀን የስራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሣሣይ ሰዓት የሚከፈት ይሆናል።
- የጨረታው አሸናፊ ያሸነፈባቸውን ዕቃዎች ለወረዳው / ፋይናንስ /ጽ/ቤት ድረስ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- የጨረታው አሸናፊ የውል ማስከበሪያ ከጠቅላላ ዋጋ 10% ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- ጽ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ከተገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፍል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ 09-16-72-17-30 ወይም 09-10-69-27-70
የሀላባ ዞን የዌራ ወረዳ ፋይ/ጽ/ቤት
