ቦሌ ማተሚያ ኃ/የተ/የግ/ማህበር bank 45 gsm 61x86 white paper, laminating film & Golden foil በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የሀገር ውስጥ የግዥ ጨረታ ማስታወቂያ
ቦሌ ማተሚያ ኃ/የተ/የግ/ማህበር bank 45 gsm 61x86 white paper, laminating film & Golden foil በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
- ተጫራቾች በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር፣ የቫት ተመዝጋቢ የምስክር ወረቀት፣ የንግድ ሰርተፊኬት እና ሌሎችም የህጋዊነት ማረጋገጫ ሰነዶችን ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች በቅድሚያ የማይመለስ ብር 100.00 /አንድ መቶ ብር/ ቢሮ ቁጥር 101 በመክፈል ለዚሁ ጨረታ የተዘጋጀውን ሰነድ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 /አስራ አምስት/ ተከታታይ ቀናት ድረስ ቦሌ መንገድ ከቶታል ነዳጅ ማደያ ዝቅ ብሎ በሚገኘው ቢሮአችን መግዛት ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስበሪያ የዋጋቸውን 2%፣ በባንክ በተረጋገጠ ቼክ /ሲፒኦ/ በቅድሚያ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ቴክኒካል እና ፋይናንሽያል ሰነዶችን በአንድ ፖስታ አሽገው ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ከግዥ ክፍል በሚገኘው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ያስገባሉ፡፡
- ተጫራቾች ለጥራት ሙከራ ይሆን ዘንድ በቂ የሆነ ናሙና ከሰነዶቻቸው ጋር አብሮ የማቅረብ ግዴታ አለባቸው፡፡
- ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባለው 15ኛው ቀን ከረፋዱ 3፡00 ሰዓት ላይ የጨረታ ሳጥኑ ታሽጐ በ3፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በማህበሩ የስብሰባ አዳራሽ ይከፈታል፡፡ የ15ኛው ቀን በዝግ ቀን ከዋለ በቀጣይ የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
- ድርጅቱ ሌላ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ስልክ ቁጥር.011515 50 05/011551 88 72
ፋክስ 011 551 86 96
ፖ.ሳ.ቁ 2365
አድራሻ፡- ቦሌ መንገድ ከቶታል ነዳጅ ማደያ ዝቅ ብሎ
አዲስ አበባ
ቦሌ ማተሚያ ኃ/የተ/የግ/ማህበር
