የደ/ም/ኢ/ክ/መ/ደ/ምዕራብ ኦሞ ዞን ቤሮ ወረዳ ፋይናንስ ኢ/ል/ጽ/ቤት በ2018 በጀት ለሴክተር መ/ቤቶች የእስቴሽነሪ፤ ፈርኒቸር እና የኤሌክትሮኒክስ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የደ/ም/ኢ/ክ/መ/ደ/ምዕራብ ኦሞ ዞን ቤሮ ወረዳ ፋይናንስ ኢ/ል/ጽ/ቤት በ2018 በጀት ለሴክተር መ/ቤቶች የእስቴሽነሪ፤ ፈርኒቸር እና የኤሌክትሮኒክስ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ስለተፈለገ በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።
- ተጫራቾች ለበጀት ዓመቱ የሚያስፈልግ የብቃት ማረጋገጫና የተሰማሩበት የስራ ዘርፍ የሚገልጽ የታደሰ ንግድ ፍቃድ ምዝገባ ፣የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸውና የዘመኑን የመንግስት ግብር የከፈሉ ፣ የታደሰ ህጋዊ ሰውነት ያላቸው ከነሰነዱ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- የተጨማሪ እሴት ታክስ (V.A.T) ተመዝጋቢ የሆኑና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN NO) ያላቸው
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ CPO በባንከ የተረጋገጠ
15,000 / አስራ አምስት ሺ ብር (ለፈርኒቸር)
15,000 / አስራ አምስት ሺ ብር (ለኤሌክትሮኒክስ)
15,000 / አስራ አምስት ሺ ብር (ለእስቴሽነሪ) ማቅረብ የሚችሉ
- ተጫራቾች ይህ ጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ስራ ቀናት ውስጥ የቤ/ሼኮ ፋ/ኢ/መምሪያ በመምጣት የማይመለስ 200 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ሰነድ መግዛት የሚችሉ ፡፡
- ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዱን ሂሳብ /ፋይናሻልና ቴክኒካል/ አንድ ዋናና 2 ኮፒ በማለት ፈርሞበት በሰም በታሸገ ኢንቨሎፐ በጨረታው ማስታወቂያ ከተመለከተው የጊዜ ገደብ በፊት በቤሮ ወረዳ ፋ/ኢ/ል/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር ለጨረታው ለተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ገቢ ማድረግ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች በእያንዳንዱ ፖስታ የሚወዳደሩበትን የስራ ቦታ፣ የድርጅቱን አድራሻ እና የተወካዩን ስልክ ቁጥር በመግለጽ መጻፍ አለበት፡፡
- ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነድ ተፈርሞበት በጥንቃቄ በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ በጨረታው ማስታወቂያው ከተመለከተው የጊዜ ገደብ በፊት የቤ/ሼኮ ፋ/ኢ/መምሪያ ለጨረታው በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ገቢ ማድረግ አለባቸው።
- ጨረታው በማስታወቂያ በወጣ በ16ኛው ቀን ከጥዋቱ 4፡00 ሰዓት ታሽጎ ከቀኑ 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
ማሳሰቢያ፡- መስሪያ ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ በከፊልም ይሁን ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
የደ/ም/ኢ/ክ/መ/ደ/ምዕራብ ኦሞ ዞን ቢሮ ወረዳ ፋይናንስ ኢ/ል/ጽ/ቤት
