በአዲስ ከተማ ጤና ጣቢያ ለ2018 በጀት አመት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ነገሮች በጨረታ አወዳድሮ ግዥ መፈጸም ይፈልጋል።
የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር 001
በአዲስ ከተማ ጤና ጣቢያ የ2018 በጀት አመት በአዲስ ዘመን በጋዜጣ በወጣው ግልጽ ጨረታ ለተጫራቾች የተዘጋጀ አገልግሎት ግዥ Lot 1 ጀነሬተር service ጥገና (ሜንቴናንስ) አወዳድሮ ለአንድ አመት ለማስጠገን ይፈልጋል፡፡ እዲሁም Lot 2 የጽህፈት መሳሪያ Lot 3 የጽዳት እቃ Lot 4 ኤሌክትሮኒክስ እና የጥገና እቃ Lot 5 ህትመት Lot 6 ደንብ ልብስ እና ስፌት Lot 7 የኮምፒውተር ጥገና Lot 8 ቋሚ እቃ Lot 9 መድሃኒት እና የህክምና እቃዎች አወዳድሮ ለመግዛት እንዲሁም Lot 10 የሽንት ቤት ቆሻሻ መጸዳጃ ማስወገድ አገልግሎት ለአንድ አመት በጨረታ አወዳድሮ ለማስወገድ ይፈልጋል፡፡
ስለዚህ በመስኩ የተሰማራችሁ አቅራቢዎች
- በዘመኑ የታደሰ ንግድ ፈቃድ
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር
- በአቅራቢዎች ዝርዝር የተመዘገበ
- የተጨማሪ እሴት ታክስ /vat/ ሰርተፍኬት ወይም TOT 2%
- በመድሀኒት ላይ የምትወዳደሩ ተጫራቾች ከኢትዮጵያ ምግብና መድህኒት ቁጥጥር ባለስልጣን ላይሰንስ ሊኖር ይገባል፡፡
- ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ግዜ ጀምሮ ተመላሽ የሚሆን የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ lot1 ጀነሬተር service 2% (3000) lot2 የጽፈት መሳሪያ 2% (4000) lot3 የጽዳት እቃ 2% (6000) lot4 ኤሌክትሮኒክስ የጥገና እቃ 2% (3000) lot5 ህትመት 2% (5000) lot6 ደንብ ልብስና ስፌት 2% (4000) lot7 የኮምፒውተር ጥገና 2% (2000) lot8 ቋሚ እቃ 2% (10000) Lot9 መድሃኒት እና የህክምና እቃዎች 2% (10000) Lot10 የሽንት ቤት ቆሻሻ መጸዳጃ ማስወገድ አገልግሎት 2% (2000) ብቻ በባንክ በተረጋገጠ /ሲፒኦ/ ከጨረታ ሰነድ ጋር በማያያዝ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ለዚሁ ጨረታ የተዘጋጀውን ዝርዝር ጉዳዮች እና የተጫራቾችን መመሪያ የያዘ ሰነድ ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የማይመለስ የጨረታ ሰነድ ብር 200 /ሁለት መቶ/ ብር በመግዛት መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ጨረታው መጀመሪያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10 የስራ ቅናት ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ እስከ 11:30 ድረስ ብቻ ማስገባት ይኖርባቸዋል ። ጨረታው የሚዘጋው በ11ኛው ቀን ከጠዋቱ 2:30 ታሽጎ 3፡00 ላይ ተጫራቶች ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- አሸናፊው ድርጅት ውል በተፈራረሙበት በ15 ቀን ውስጥ እቃውን ያቀርባል፡፡
- አሸናፊ ሆኖ የተመረጠው ድርጅት በአካል በመቅረብ ስራውን ማከናወን አለበት።
- ጨረታው ከተከፈተ ተጫራቾች ባቀረቡት የመወዳደሪያ ሀሳብ ላይ ለውጥ ወይም ማሻሻያ ማድረግ ወይም ከጨረታው እራሳቸውን ማግለል አይችሉም፡፡
- ተጫራቾች የዋጋ ዝርዝራቸውን በገዙት የጨረታ ሰነድ ላይ ብቻ ሞልተው እና በእያንዳንዱ ገጽ ላይ ማህተም በማድረግ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- የጨረታው አሸናፊ የሆነው ግለሰብም ሆነ ድርጅት ውል በሚያዝበት ወቅት ያሸነፈበትን የሽያጭ ቅላላ ዋጋ 10% የውል ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዛዝ (cpo) ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾቾ በገዙት ሰነድ መሰረት የሚወዳደሩበትን ዋጋ 15% vat ያካተተ መሆኑን ወይም አለመሆኑን መጠቀስ ይኖርበታል፡፡ ካልተጠቀሰ እንደተካተተ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡
- ኦርጅናል ሰነድ ከሙሉ ሰነድ ጋር እና ኮፒውን ሰነድ ለየብቻ ተደርጎ በማያያዝ ማስገባት ይኖርባቸዋል። እንዲሁም የድርጅቱ ማህተም እያንዳንዱ ሰነዶች ላይ መደረግ አለበት፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ ለሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ማንኛውም ተጫራች መደበኛ የጨረታ ሰነዱን የሚሞሉ ክፍሎችን በአግባቡ ሞልቶ ተመላሽ ያላደረገ አቅራቢ ቅድመ ምርመራ ጨረታ ላይ ውድቅ ይደረጋል።
- የጥቃቅንና አነስተኛ የተደራጀ ልዩ አስተያየት የሚደረገው በሚያመርቱት ምርት ብቻ ሆኖ ከተደራጁበት ተቋም በሚያቀርቡት ደብዳቤ ይሆናል፡፡
ተጨማሪ መረጃ
የጨረታ ሰነድ የሚገኝበት ቦታ አ/ከ/ክ/ከ/ጤና ጣቢያ መሳለሚያ እህል በረንዳ ከእሳት አደጋ በስተጀርባ በሚገኘው ግዥ ቢሮ ቁጥር 5 በአካል በመቅረብ መውሰድ ይችላሉ፡፡
ለበለጠ መረጃ ደውለው መየት ይችላሉ ስልክ ቁጥር 0112756204
የአዲስ ከተማ ጤና ጣቢያ
