የሳሪስ ልማተ ገበያ አዲስ ህይወት አክሲዮን ማህበር የፋይናንስ ሲስተሙን ከGAAP ወደ IFRS ሲስተም መቀየር እንዲሁም Asset Valuation and implimentation training በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ በአሸናፊው ተጫራች በመታገዝ ሲስተሙን መቀየር ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የሳሪስ ልማተ ገበያ አዲስ ህይወት አክሲዮን ማህበር የፋይናንስ ሲስተሙን ከGAAP ወደ IFRS ሲስተም መቀየር እንዲሁም Asset Valuation and implimentation training በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ በአሸናፊው ተጫራች በመታገዝ ሲስተሙን መቀየር ይፈልጋል።
የጨረታው መሰፈርቶች
- የጨረታ ዓይነት From GAAP to IFRS Conversion, Asset Valuation and implimentation training
- በዘርፉ የተሠማሩ ሕጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ የንግድ ምዝገባ የምስክር ወረቀት፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ እና የተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡበት ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው።
- ተጫራቾች በጨረታ ሠነዳቸው የሚያሰማሩዋቸውን ባለሙያዎች የብቃት ማረጋገጫና የሚሰጧቸውን አገልግሎቶች ዝርዝር ሥራ ቀደም ሲል የመቀየር ሥራ የሠሩባቸውን ዝርዝርና የምስጋና ወረቀት ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
- ተጫራቾች ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 የሥራ ቀናት ውስጥ አክሲዮን ማህበሩ ጽ/ቤት በመቅረብ የጨረታ ሠነድ የማይመለስ ብር 200.00 (ሁለት መቶ ብር) ከፍለው በመግዛት መጫረት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን የጨረታ ቴክኒካልና ፋይናንሻል ሠነድ በሁለት ፖስታዎች በሰም በታሸገ ኤንቭሎፕ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው ነሐሴ 13 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ተዘግቶ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው፣ በተገኙበት ከቀኑ 8፡30 በአ.ማ የዳይሬክተሮች ቦርድ ቢሮ ይከፈታል።
- የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ብር 20,000 (ሃያ ሺህ ብር) በባንክ በተረጋገጠ ቼክ (unconditional Bank Guarantee) ከማመልከቻ ሠነዳቸው ጋር ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች ሠርተው የሚያስረክቡበትን ጊዜ በጨረታ ሠነድ ላይ መጥቀስ ይጠበቅባቸዋል።
- አክሲዮን ማህበሩ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- አቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር ከሬስ ኢንጅነሪንግ አ/ማ አጠገብና የሳሪስ ባቡር ተርሚናል ፊት ለፊት፣
ለበለጠ ማስረጃ፡- የስልክ ቁጥር +251-114422121
