ፀደይ ባንክ አ.ማ በአዲስ አበባ ከተማ፣ ልደታ ክፍለ ከተማ፣ ወረዳ 07(ሰንጋ ተራ አካባቢ) ባስገነባው 4B+G+M+25 ህንጻ ውስጥ፡-ከምድር ወለል ጀምሮ እስከ 6ኛ ፎቅ ለንግድ ስራ (ለሱቅ፣ለሬስቶራንት፣ ለፋርማሲ፣ለሜዲካል ሴንተር፣ለውበት ሳሎን፣ካፌ፣ሱፐር ማርኬት፤ ሾው /ዲስፕለይ ሩም ወዘተ) አገልግሎት የተዘጋጁ ከፍሎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማከራየት ይፈልጋል፡፡
የህንፃ ኪራይ የጨረታ ማስታወቂያ
ፀደይ ባንክ አ.ማ በአዲስ አበባ ከተማ፣ ልደታ ክፍለ ከተማ፣ ወረዳ 07(ሰንጋ ተራ አካባቢ) ባስገነባው 4B+G+M+25 ህንጻ ውስጥ፡-ከምድር ወለል ጀምሮ እስከ 6ኛ ፎቅ ለንግድ ስራ (ለሱቅ፣ለሬስቶራንት፣ ለፋርማሲ፣ለሜዲካል ሴንተር፣ለውበት ሳሎን፣ካፌ፣ሱፐር ማርኬት፤ ሾው /ዲስፕለይ ሩም ወዘተ) አገልግሎት የተዘጋጁ ከፍሎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማከራየት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም፡-
1. ተጫራቾች የማይመለስ ብር 500.00 /አምስት መቶ ብር/ ፀደይ ባንክ ለገሀር ቅርንጫፍ ወይም በማንኛውም የፀደይ ባንከ ቅርንጫፍ በመከፈል የጨረታ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ጳጉሜ 03 ቀን 2017 ዓ.ም ጨረታው እስከሚዘጋበት ድረስ መ/ቤቱ በመቅረብ ዘወትር በስራ ሰዓት ከሰኞ እስከ ዓርብ ከ2፡00 እስከ 11፡00 ሰዓት እና ቅዳሜ እስከ 6፡00 ሰንጋ ተራ በሚገኘው ፀደይ ባንክ ኢማ ዋና መ/ቤት 16ኛ ፎቅ ግዥ ከፍል መውሰድ ይችላሉ፡፡ ጨረታው የሚከፈትበት ቦታና ሰዓት ሰንጋ ተራ አካባቢ በሚገኘው ፀደይ ባንክ አ.ማ ዋና መ/ቤት 5ኛ ፎቅ በሚገኘው የስብሰባ አዳራሽ ሲሆን የጨረታው መዝጊያ ቀን ጳጉሜ 03 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ሲሆን የጨረታ መክፈቻ በተመሳሳይ ቀን ጳጉሜ 03 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት ላይ ይሆናል።
2. ተጫራቾች ከአንድ በላይ በሆኑ ከፍሎች መሳተፍ ይችላሉ። ሆኖም የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የሚወዳደሩበትን ክፍሎች ካሬ ሜትር ጠቅላላ የሶስት ወር የቅድሚያ ከፍያ የኪራይ ዋጋ መነሻ በማድረግ 2% ወይም የጠቅላላ ዋጋው 2% ከብር 500,000.00 የሚበልጥ ከሆነ ብር 500,000.00 በባንከ የተረጋገጠ የክፍያ ትእዛዝ (ሲ.ፒ.ኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) በፀደይ ባንከ ኢማ ስም ማስያዝ አለባቸው፡፡
3. ተጫራቾች ነጋዴዎች ከሆኑ የታደሰ እና አግባብነት ያለው የንግድ ስራ ፈቃድ፣ የግብር ከፋይ የምስከርወረቀት ማቅረብ የሚችሉ እንዲሁም ለትርፍ ያልተቋቋሙ ድርጅቶች ከሆኑ የታደሰ የምዝገባ ሰነድ ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው።
4. ተጫራቾች ህንጻውን (ከፍሉን) ለምን ዓላማ እንደሚከራዩት መግለጽ አለባቸው፡፡
5. ተጫራቾች ለኪራይ የቀረቡ ከፍሎችን በተዘጋጀው የዋጋ ማቅረቢያ ሰንጠረዥ ላይ በተገለፀው ቦታ ከነሐሴ 05 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ጳጉሜ 03 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ በስራ ቀን እና ሰዓት አዲስ አበባ ህንፃው ባለበት ቦታ በመገኘት ማየት ይችላሉ፡፡
6. የጨረታው አሸናፊ የሚሆነው ለከፍሎች በተሰጣቸው መለያ ቁጥር መሰረት በሜትር ካሬ ከፍተኛ ዋጋ ያቀረበ ተጫራች ይሆናል።
7. ተጫራቾች በፖስታቸው ላይ ስም፣ ፊርማና ስልከ ቁጥር መፃፍ አለባቸው።
8. ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0918 78 21 88 /0911383713 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡
9 ባንኩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠ ነው።
አድራሻ፡- አዲስ አበባ ከተማ ሰንጋተራ አካባቢ በሚገኘው የባንኩ ዋና መ/ቤት ህንጻ 16ኛ ፎቅ ቁጥር 09
ፀደይ ባንክ አ.ማ
