ፀደይ ባንክ አ.ማ በአዲስ አበባ ከተማ፣ ልደታ ክፍለ ከተማ፣ ወረዳ 07 (ሰንጋተራ አካባቢ) ባስገነባው 4B+G+M+25 ህንጻ ውስጥ፡- ከምድር ወለል ጀምሮ እስከ 6ኛ ፎቅ ለንግድ ስራ (ለሱቅ፣ ለሬስቶራንት፣ ለፋርማሲ፣ ለሜዲካል ሴንተር፣ ለውበት ሳሎን፣ ካፌ፣ ሱፐር ማርኬት፤ ሾው /ዲስፕለይ ሩም ወዘተ) አገልግሎት የተዘጋጁ ክፍሎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማከራየት ይፈልጋል።
የህንፃ ኪራይ የጨረታ ማስታወቂያ
ፀደይ ባንክ አ.ማ በአዲስ አበባ ከተማ፣ ልደታ ክፍለ ከተማ፣ ወረዳ 07 (ሰንጋተራ አካባቢ) ባስገነባው 4B+G+M+25 ህንጻ ውስጥ፡- ከምድር ወለል ጀምሮ እስከ 6ኛ ፎቅ ለንግድ ስራ (ለሱቅ፣ ለሬስቶራንት፣ ለፋርማሲ፣ ለሜዲካል ሴንተር፣ ለውበት ሳሎን፣ ካፌ፣ ሱፐር ማርኬት፤ ሾው /ዲስፕለይ ሩም ወዘተ) አገልግሎት የተዘጋጁ ክፍሎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማከራየት ይፈልጋል።
በመሆኑም፡-
- ተጫራቾች የማይመለስ ብር 500.00 /አምስት መቶ ብር/ ፀደይ ባንክ ለገሀር ቅርጫፍ ወይም በማናኛውም የፀደይ ባንክ ቅርንጫፍ በመክፈል የጨረታ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ጳጉሜን 03 ቀን 2017 ዓ.ም ጨረታው እሰከሚዘጋበት ድርስ መ/ቤቱ በመቅረብ ዘወትር በስራ ስዓት ከሰኞ እስከ አርብ ከ2፡00 እስከ 11፡00 ሰዓት እና ቅዳሜ እስከ 6፡00 ሰንጋተራ በሚገኘው ፀደይ ባንክ አ.ማ ዋና መ/ቤት 16ኛ ፎቅ ግዢ ክፍል መውሰድ ይችላሉ። ጨረታው የሚከፈትበት ቦታና ሰዓት ሰንጋተራ አካባቢ በሚገኘዉ ፀደይ ባንክ አ.ማ ዋና መ/ቤት 5ኛ ፎቅ በሚገኘው የስብሰባ አዳራሽ ሲሆን የጨረታው መዝጊያ ቀን ጳጉሜን 03 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ሲሆን የጨረታ መክፈቻ በተመሳሳይ ቀን ጳጉሜ 03 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:30 ሰዓት ላይ ይሆናል፡፡
- ተጫራቾች ከአንድ በላይ በሆኑ ክፍሎች መሳተፍ ይችላሉ። ሆኖም የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የሚወዳደሩበትን ክፍሎች ካሬ ሜትር ጠቅላላ የሶስት ወር የቅድሚያ ክፍያ የክራይ ዋጋ መነሻ በማድረግ 2% ወይም የጠቅላላ ዋጋው 2% ከብር 500,000.00 500,000.00 በባንክ የተረጋገጠ የክፍያ ትእዛዝ (ሲ.ፒ.ኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) በፀደይ ባንክ አ.ማ ስም ማስያዝ አለባቸው።
- ተጫራቾች ነጋዴዎች ከሆኑ የታደሰ እና አግባብነት ያለው የንግድ ስራ ፈቃድ፤ የግብር ከፋይ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ እንዲሁም ለትርፍ ያልተቋቋሙ ድርጅቶች ከሆኑ የታደሰ የምዝገባ ሰነድ ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው።
- ተጫራቾች ህንጻዉን (ክፍሉን) ለምን ዓላማ እንደሚከራዩት መግለጽ አለባቸው።
- ተጫራቾች ለኪራይ የቀረቡ ክፍሎችን በተዘጋጀው የዋጋ ማቅረቢያ ሰንጠረዥ ላይ በተገለፀው ቦታ ከነሐሴ 05 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ጳጉሜን 03 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ በስራ ቀን እና ሰዓት አዲስ አበባ ህንፃው ባለበት ቦታ በመገኘት ማየት ይችላሉ።
- የጨረታው አሸናፊ የሚሆነዉ ለክፍሎች በተሰጣቻው መለያ ቁጥር መሰረት በሜትር ካሬ ከፍተኛ ዋጋ ያቀረበ ተጫራች ይሆናል።
- ተጫራቾች በፖስታቸው ላይ ስም፣ ፊርማና ስልክ ቁጥር መፃፍ አለባቸው።
- ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0918 78 21 88 /0911 38 37 13 በመደወል ማግኘት ይችላሉ።
- ባንኩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- አዲስ አበባ ከተማ፤ ሰንጋተራ አካባቢ በሚገኘው የባንኩ ዋና መ/ቤት ህንጻ 16ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 09
ፀደይ ባንክ አ.ማ
