የአዳማ ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በ2018 የበጀት ዓመት የተለያዩ ዕቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ለአንደኛ ጊዜ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
የአዳማ ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በ2018 የበጀት ዓመት:-
- ለግቢ ውስጥ መድኃኒቶች እና የህክምና ዕቃዎች
- ለኮሚኒቲ ፋርማሲ መድኃኒቶች እና
- የፈርኒቸር እቃዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
በመሆኑም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ነጋዴዎች መወዳደር ትችላላችሁ።
- የ2017 ዓ.ም የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ በዘርፉ ያላችሁ።
- ተጫራቾች የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ተመዝጋቢ ስለመሆኑ መረጃ ማቅረብ የሚችል።
- በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ፅ/ቤት በአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ መመዝገባቸውን የሚያረጋግጥ መረጃ ማቅረብ የሚችሉ ።
- ተጫራቾች ያሸነፉበትን ዕቃ ገዥ መ/ቤት ድረስ በራሳቸው ወጪ ማቅረብ የሚችሉ።
- ተጫራቾች የሚያቀርቡትን የጨረታ ሰነድ ኮፒና ኦሪጅናል ለየብቻ በተለያየ ፖስታ ማሸግ አለባቸው።
- ስርዝ ድልዝ ያለው፤ የማይታይ የጨረታ ሰነድ ወይም የዋጋ ዝርዝር ተቀባይት የለውም።
- ጨረታውን ከአሸነፈ በኋላ የውል ማስከበሪያ የአሸነፈበትን ዋጋ 10% ማስያዝ የሚችል።
- ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ከኮሌጁ ግዥና ፋይናንስ የስራ ሂደት ከፍል ዘወትር በስራ ሰዓት የማይመለስ ለመድኃኒቶች በእያንዳንዱ ጨረታ 500 /አምስት መቶ ብር/ እና ለፈርኒቸር እቃዎች 200 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መውሰድ አለባቸው።
- የመድኃኒቶች እና የህክምና እቃዎች ጨረታው የሚከፈተው በ20/12/2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:30 ተጫራቾች /ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
- የኮሚኒቲ ፋርማሲ መድኃኒቶች ጨረታው የሚከፈተው በ21/12/2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:30 ተጫራቾች /ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
- የፈርኒቸር እቃዎች ጨረታው የሚከፈተው በ21/12/2017 ዓ.ም ከቀኑ 9:30 ተጫራቾች /ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
- ተጫራቾች የሚሞሉትን ዋጋ በመስሪያ ቤቱ ሰነድ ብቻ ላይ መሆን አለበት።
- ጨረታ ማስከበሪያ
- ለግቢ ውስጥ መድኃኒቶች እና የህክምና እቃዎች እና በኮሚኒቲ ፋርማሲ መድኃኒቶች ለየ ብቻ 30,000 (ሰላሳ ሺህ ) ብር
- ለፈርኒቸር እቃዎች 20,000 (ሃያ ሺህ) ብር በ"CBE, CBO, እና በSinqee" ባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ብቻ ማስያዝ የሚችል መሆን አለበት።
- መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታው በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብት የተጠበቀ ነው።
አዳማ ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ
