ሲዳማ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን የ2017 ዓ/ም በጀት ዓመት ሒሳብ ሰነድ በጨረታ አወዳድሮ ማስመርመር ወይም ኦዲት ማስደረግ ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
ሀገር አቀፍ ግልፅ ጨረታ ቁጥር 04/2017
ሲዳማ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን የ2017 ዓ/ም በጀት ዓመት ሒሳብ ሰነድ በጨረታ አወዳድሮ ማስመርመር ወይም ኦዲት ማስደረግ ይፈልጋል፡፡
በመሆኑም በጨረታው ለመሳተፍ የሚችሉ ተጫራቾች፡-
- በዘርፉ የታደሰ ህጋዊ ፍቃድ ያላቸው
- ቫት የተመዘገቡ
- በጨረታ ለመሣተፍ ከገቢዎች ፍቃድ ያላቸው
- የመልካም ሥራ አፈፃፀም ማስረጃ ያላቸው መሆን ይኖርባቸዋል
- የጨረታ ሰነድ የሚሸጥበት ጊዜና ቦታ፡-
- ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15 ተከታታይ ቀናት ድረስ የማይመለስ ብር 300.00 /ሶስት መቶ ብር/ በሲዳማ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን የሂሳብ ቁጥር 1000604259658 በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ገቢ በማድረግ የንግድ ፍቃዳቸውን ፎቶ ኮፒ ይዘው በመቅረብ ከግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬከቶሬት የጨረታ ሰነድ መግዛት ይችላሉ፣
- ጨረታው የሚከፈትበት እና ሰነዱ የሚቀርብበት ጊዜ፡-
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳቸውን ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ16ኛው ቀን ከቀኑ ከ8፡30 እስከ 11፡00 ሰዓት በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ያስገባሉ።
- በማግስቱ በ17ኛው ቀን ከጧቱ ከ3፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- ዕለቱ የስራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን ይከፈታል፡፡
- የጨረታ ዋስትና፡-
- ማንኛውም ተጫራች 2% በባንክ የተረጋገጠ CPO ወይም ከስድስት ወር ያላነሰ ጊዜ ያለው በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ ቢድ ቦንድ ዋስትና ከዋጋ ማቅረቢያ ጋር አያይዞ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
- የጨረታ ሠነድ አስተሻሸግ ሁኔታ፡-
- የዘመኑ የታደሰ የንግድ ፍቃድ ማስረጃ ፣ የልዩ እሴት ታክስ ተመዝጋቢነትና የታክስ ክፍያ ማረጋገጫ ሰነዶች ፣ በጨረታው ለመሳተፍ ከገቢዎች የተሰጠ ማስረጃ እና የጨረታ ማስከበርያ በባንክ የተደገፈ CPO/ ከኦርጂናል የዋጋ ማቅረቢያ ጋር በአንድ ላይ በሰም ታሽገው መቅረብ አለባቸው፡፡ ፋይናንሻል ዶክሜንት ኦርጅናልና ኮፒ ለየብቻ በሰም ታሽጎ መቅረብ ይኖርበታል፡፡
- ቴክኒካል ዶክመንት ኦርጅናልና ኮፒ ለየብቻ በሰም ታሽጎ መቅረብ ይኖርበታል፡፡
ይህንን አስተሻሸግ ዘዴ ያልተጠቀመ ተጫራች ከጨረታው ይሠረዛል፡፡
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0916071539 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
ኮርፖሬሽኑ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
የሲዳማ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ሲኮስኮ)
