የኮልፌ ቅዱስ ራጉኤል አዲስ ሕይወት አክሲዮን ማኅበር ለ3 ዓመት የአክሲዮን ማኅበሩን ሂሳብ በውጭ ኦዲተር አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡
የኦዲት ሥራ የጨረታ ማስታወቂያ
የኮልፌ ቅዱስ ራጉኤል አዲስ ሕይወት አክሲዮን ማኅበር ለ3 ዓመት የአክሲዮን ማኅበሩን ሂሳብ በውጭ ኦዲተር አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡
ስለዚህ ማንኛውም ከዚህ በታች የተገለፁት መስፈርቶችን የምታሟሉ ተጫራቾች በጨረታው መጫረት የምትችሉ መሆኑን እንገለፃለን፡፡
- የንግድ መለያ ቁጥር፡፡
- የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት፡፡
- የታደሰ የንግድ ፈቃድ፡፡
- የብቃት ማረጋገጫ፣ የሥራ ልምድ ማሳየት ወይም መረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- የAABE መረጃ የሚያቀርብ (የኢትዮጲያ ሂሳብ አያያዝና አዲት ቦርድ የምዝገባ ምስክር ወረቀት) ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ወይም የሚያቀርቡትን ዋጋ በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 (አስር) ተከታታይ የሥራ ቀናት ጠዋት 2፡30 ሰዓት እስከ 6፡30 ሰዓት ከሰዓት ከ7፡30 ሰዓት እስከ 10፡30 ሰዓት ሙሉ መረጃቸውን ኦርጅናሉንና ኮፒ በመያዝ በኮልፌ ቅዱስ ራጉኤል አዲስ ሕይወት አክሲዮን ማኅበር ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 1/4 ማስገባት ትችላላችሁ።
- አድራሻ :- ኮልፌ አጠና ተራ ከቴሌ ኮሙኒኬሽን ጀርባ የኮልፌ ቅዱስ ራጉኤል አዲስ ሕይወት አክሲዮን ማኅበር ብሎክ 2 አ4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 4
- ስልክ፡- 09-63-87-10-45 ወይም 09-32-08-03-77
ኮልፌ ቅዱስ ራጉኤል አዲስ ሕይወት አክሲዮን ማኅበር
