ኩባንያችን ብሔራዊ የኢትዮጵያ ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የሳይቱ ስም ቦሌ አያት አንድ ሳይት 2 የሚገኘውን የ40/60 ኮንደሚኒየም የንግድ ቤት በጨረታ አወዳድሮ ማከራየት ይፈልጋል።
ብሔራዊ የኢትዮጵያ ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ.
National Insurance Company of Ethiopia S.C.
የንግድ ቤት ኪራይ ጨረታ
የጨረታ ቁጥር 01/25
ኩባንያችን ብሔራዊ የኢትዮጵያ ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የሳይቱ ስም ቦሌ አያት አንድ ሳይት 2 ሕንፃ ቁጥር 38 የወለል ቁጥር 1ኛ የቤት ቁጥር BA152/B-38/SN/107 የቤቱ ሥፋት ከነቴራስ 194.94፤ የጋራ መጠቀሚያ ስፋት 74.01 ካሬ ሜትር ጠቅላላ ስፋቱ 268.95 ካሬ ሜትር የሆነውን የ40/60 ኮንደሚኒየም የንግድ ቤት በጨረታ አወዳድሮ ማከራየት ይፈልጋል።
ስለሆነም፡-
- የኪራይ ቤቱ አድራሻ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የሳይቱ ስም ቦሌ አያት አንድ ሳይት 2 ሕንፃ ቁጥር 38 የወለል ቁጥር 1ኛ የቤት ቁጥር BA152/B-38/SN/107 በተለምዶ አጠራሩ ከአያት 49 ወደ አራብሳ ኮንደሚኒየም በሚወስደው መንገድ ወደ ኖህ ሪል እስቴት በሚወስደው መስቀለኛ መንገድ ላይ የመጀመሪያ ህንጻ ላይ የሚገኝ ሲሆን ተጫራቾች ከመስከረም 5 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ መስከረም 21 ቀን 2018 ዓ.ም. 4:00 የሚከራየውን ቤት መመልከት ይችላሉ፡፡
- የጨረታ መነሻ ዋጋ በካሬ ከተ.እ.ታ. በፊት ብር 400.00 /አራት መቶ ሲሆን/ አጠቃላይ የሚታሰበው ካሬ 268.95 ይሆናል፡፡
- ተጫራቾች የታደሰ የንግድ ፈቃድ ሰርትፍኬት ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ዋጋ ተ.እ.ታ ሳይጨምሩ በዋጋ ማቅረቢያ ቅፅ ላይ በመሙላት ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ብር 10,000.00 /አስር ሺህ ብር/ ብሔራዊ የኢትዮጵያ ኢንሹራንስ ኩባንያ (አ.ማ.) ወይም በእንግሊዝኛ NATIONAL INSURANCE CO. OF ETHIOPIA (S.C.) ስም በማንኛውም ባንክ በተረጋገጠ ቼክ (CPO) በማስራት ከዋጋ ማቅረቢያ ጋር በኤንቨሎፕ በማሽግ ከመስከረም 5 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ መስከረም 21 ቀን 2018 ዓ.ም. 4:00 ሰዓት ላንቻ ባቡር ጣቢያ ፊት ለፊት ዘፍኮ ሕንፃ በሚገኘው በዋናው መ/ቤት 5ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 8 በሚገኘው የሰው ሀብትና ፋሲሊቲ ሥራ አመራር መምሪያ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ፡፡
- የጨረታ አሸናፊው ከኩባንያችን ጋር ህጋዊ ውል የሚፈጽም ሲሆን ዝቅተኛው የኪራይ ክፍያ የ6 /ስድስት/ ወር በአንድ ጊዜ መክፈል ይኖርበታል፡፡
- የጨረታ አሸናፊው ከኩባንያችን ጋር ውል የሚፈጽመው በጨረታ ወቅት ባስገባው የንግድ ፈቃድ ስም ሲሆን የኪራይ ቤቱን ለሶስተኛ ወገን አሳልፎ መስጠት አይቻልም።
- ጨረታው መስከረም 21 ቀን 2018 ዓ.ም. ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ በዕለቱ ጠዋት በ4፡30 ሰዓት ላይ ላንቻ ባቡር ጣቢያ ፊት ለፊት ዘፍኮ ሕንፃ በሚገኘው በዋናው መ/ቤት 5ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 8 በሚገኘው የሰው ሀብትና ፋሲሊቲ ሥራ አመራር መምሪያ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
- ኩባንያው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብት አለው።
ብሔራዊ የኢትዮጵያ ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ
ስልክ 011-466-11-29/0114-65-56-05
