ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ለተለያዩ ተሽከርካሪዎች አገልግሎት የሚውል ጎማዎች፣ የወርክሾፕ ማሸነሪዎች፣ የኤከስካቫተር ጃክሀመር እንዲሁም የኤክስካቫተር አካፋ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
ጨረታ ቁጥር ዘመን /ማሽግ 03/2018
ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ለተለያዩ ተሽከርካሪዎች አገልግሎት የሚውል ጎማዎች፣ የወርክሾፕ ማሸነሪዎች፣ የኤከስካቫተር ጃክሀመር እንዲሁም የኤክስካቫተር አካፋ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
- ሎት 1 የተለያዩ ተሽከርካሪ ጎማዎች
- ሎት 2 የወርክ ሾፕ ማሸነሪዎች ሎት
- የኤክስካቫተር ጃክ ሀመር
- ሎት 4 የኤክስካቫተር አካፋ
ስለሆነም በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች መሳተፍ የሚችሉ መሆኑን እየገለጽን፤
- በዘርፉ ለዘመኑ የታደሰ የንግድ ስራ ፈቃድና፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር (TIN) እና የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ የምስከር ወረቀት ያለው/ያላት
- የጨረታ ማስከበሪያ የጠቅላላ ዋጋውን ቫትን ጨምሮ 2% በባንክ በተረጋገጠ ሲ.ፒ.ኦ (CPO) ወይም /unconditional bank guarantee/ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማስያዝ ይኖርበታል፣
- የጨረታ ሰነዱን ባ/ዳር ከተማ ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ቀበሌ 11 እና አ/አበባ ለገሀር አመልድ ኢትዮጵያ ህንጻ 7ኛ ፎቅ በሚገኘው ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ቢሮ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 200.00 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት መውሰድ ይችላሉ፡፡
- የጨረታ መዝጊያ እና መክፈቻ ቀናት ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ሰነዶች ኦርጅናልና ኮፒውን በመለየት በተለያዩ ፖስታዎች በጥንቃቄ በማሸግ ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እሰከ 15ኛው ቀን (15 ተከታታይ ቀናት በመቁጠር) ድረስ ብቻ ዘመን ኮንስትራክሽን የማሽ/ተሽ/መ/ግዥና አቅ/ኬዝ ቲም ቢሮ (ባህር ዳርዩኒቨርሲቲ ጥበብ ህንጻ አካባቢ የቀድሞው የአማራ ከተሞች ልማት አ.ማ ግቢ ውስጥ) በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው በ15ኛው ቀን በተራ ቁጥር 4 በተገለጸው ቦታ በ8፡00 ሰዓት ሳጥኑ ታሽጎ 8፡30 ይከፈታል፡፡ የመዝጊያና መክፈቻ ቀኑ የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን እስከ ቀኑ 8፡00 ሰዓት ድረስ ማስገባት የሚችሉ ሲሆን በዚያኑ ቀን 8፡00 ሰዓት ሳጥኑ ታሽጎ 8፡30 ይከፈታል፡፡
- ዝርዝር የጨረታ መመሪያውን እና የውል ይዘቱን እንዲሁም የሚገዙትን እቃዎችና አገልግሎቶች፣ ዝርዝር ቴክኒከል መገምገሚያዎች በሙሉ ከጨረታ ሰነዱ ውስጥ የተገለፀ ስለሆነ ማንኛውም ተጫራች በጥንቃቄ በማንበብ ዋጋቸውን በጨረታ መመሪያው መሰረት መሙላት አለበት፡፡
- ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
ስልክ ቁጥር:- 058-3205185/0918715641/0927605599
ፋክስ: - 058-218-0538/058-320-4001
ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን
