የግል ድርጀት ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር ከዚህ በታች የቀረቡትን ዕቃዎች እና አገልግሎቶች ማለትም የተለያዩ ልዩ ልዩ መሣሪያዎች፣ ቋሚ የቢሮ ዕቃዎች /ፈርኒቸር፣ የተሽከርካሪ ጎማዎች እና ማስዋቢያ ዕቃዎች ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የግል ድርጀት ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር ከዚህ በታች የቀረቡትን ዕቃዎች እና አገልግሎቶች ማለትም የተለያዩ ልዩ ልዩ መሣሪያዎች፣ ቋሚ የቢሮ ዕቃዎች /ፈርኒቸር፣ የተሽከርካሪ ጎማዎች እና ማስዋቢያ ዕቃዎች ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
በዚሁ መሰረት ከዚህ በታች የተገለፀውን መስፈርት የሚያሟሉ ተጫራቾች በጨረታው እንዲወዳዳሩ ተጋብዘዋል።
- በዘርፉ ህጋዊ የታደሰ የንግድ ፍቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉ እና በጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችል ማስረጃ (ክሊራንስ) ማቅረብ አለባቸው።
- የተጨማሪ እሴት ታክስ /VAT/ ተመዝጋቢ የሆኑ እና የንግድ መለያ ቁጥር (TIN) ያላቸው መሆን ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የአቅራቢነት የምስክር ወረቀት ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የብቃት ማረጋገጫ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ማንኛውም ተጫራች ጨረታው ከተከፈተ በኋላ በጨረታው ሰነድ ላይ የተገለጸውን ማናቸውንም ሁኔታዎች መለወጥ ወይም ማሻሻል ወይም ከጨረታው መውጣት አይችልም።
- የሚገዙ ዕቃዎች በተሰጠው ስፔስፊኬሽን(ልዩ ልዩ መሣሪያዎች፣የተሽከርካሪ ጎማዎች እና ማስዋቢያ ዕቃዎች) ተወዳዳሪ ድርጀቶች ናሙና /ሳምፕል /ጨረታው ከመከፈቱ በፊት በአስተዳደሩ ንብረት ክፍል ማስገባት ይኖርባቸዋል። ዕቃዎች ሙሉ በሙሉ ኦሪጅናል መሆን አለባቸው።
- ቋሚ የቢሮ ዕቃዎች (ፈርኒቸር) አስተዳደሩ በሚያቀርበው ናሙና/ሳምፕል መሰረት አሟልቶ ላልቀረበ ማንኛውም ሁኔታዎች ስህተት ቢፈጸም ኃላፊነቱ የተጫራቾች /የአቅራቢው/ ድርጅት ይሆናል።
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተመሰከረለት CPO /ሲፒኦ/ ወይም የባንክ ዋስትና በአስተዳደሩ ስም ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 400 /አራት መቶ ብር/ በመክፈል መግዛት ይችላሉ።
- የጨረታ ሰነዱን ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ሲሆን ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ከጠዋቱ 2፡00 እስከ ቀኑ 11፡00 ድረስ መግዛት ይችላሉ። ጨረታው በ16ኛው የስራ ቀን በ4፡00 ታሽጎ በዚያው ዕለት በ 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። ይሁን እንጂ 16ኛው ቀን የሥራ ቀን ካልሆነ በቀጣዩ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል።
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ ዋናውንና ኮፒውን የቴከኒክና ፋይናንስ ሰነዶችን በተናጠል በታሸገ ኤንቨሎፕ የድርጅቱን ማህተም በማድረግ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ለጨረታው የሚቀርበው ሰነድ ስርዝ ድልዝ የሌለበት ሆኖ የሚቀርበው ዋጋ በግልጽ መጻፍ ይኖርበታል። ስርዝ ድልዝ ወይም አሻሚ የሆነ ዋጋ ከቀረበ ተጫራቹ ከውድድር ውጪ ይደረጋል።እንዲሁም በአስተዳደሩ ተዘጋጅቶ በጨረታ ሰነድ ላይ ብቻ ዋጋ መሞላት አለበት።
- አሸናፊ ድርጅት ባሸነፈባቸው ዕቃዎች ከጠቅላላ ዋጋ 10% ለድርጅቱ ውል ማስከበሪያ ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው አሸንፎ በወቅቱ ውል ለማሰር ፈቃደኛ ያልሆነ ተጫራች በጨረታ ያስያዘው የጨረታ ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ /cpo/ሲፒኦ/ ለአስተዳደሩ ገቢ ይደረጋል። አስፈላጊው አሰተዳደራዊ እርምጃ ይወሰዳል።
- አስተዳደሩ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
|
ተ.ቁ
|
የግዥው ዓይነት
|
የጨረታ ቁጥር
|
የጨረታ ማስከበሪያ የገንዘብ መጠን
|
|
ሎት 1
|
ልዩ ልዩ መሣሪያዎች
|
የግድሠማዋአ /ብግጨ/001/007/2018
|
50,000.00 / ሃምሳ ሺህ ብር /
|
|
ሎት 2
|
የተሽከርካሪ ጎማዎች
|
የግድሠማዋአ /ብግጨ/001/08/2018
|
150,000 / አንድ መቶ ሃምሳ ሺህ ብር /
|
|
ሎት 3
|
ቋሚ የቢሮ ዕቃዎች/ፈርኒቸር /
|
የግድሠማዋአ /ብግጨ/001/09/2018
|
100,000.00 / አንድ መቶ ሺህ ብር /
|
አድራሻችን፡- አዲስ አበባ መገናኛ ቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ፊት ለፊት ወይም የአስተዳደሩ ዋና መ/ቤት የግዥ ዳይሬክቶሬት 11ኛ ፎቅ
ለበለጠ ማብራሪያ ስልክ ቁጥር +251-111-56 88 90
የግል ድርጀት ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር
