የኦሮሚያ ምርጥ ዘር ኢንተርፕራይዝ የ2017 የበጀት ዓመት ሂሳብ በውጪ ኦዲት አገልግሎት "External Audit Service" በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሠራት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር OSE/ NCB/008/2018
የኦሮሚያ ምርጥ ዘር ኢንተርፕራይዝ የ2017 የበጀት ዓመት ሂሳብ በውጪ ኦዲት አገልግሎት "External Audit Service" በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሠራት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም አስፈላጊውን መስፈርት የምታሟሉ በጨረታው መሳተፍ የሚትችሉ መሆኑን እየገለጽን ተጫራቾች፡-
- የንግድ ምዝገባ ሰርተፍኬት፣ የዘመኑን የታደሰ ንግድ ፈቃድ፣
- የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ ሰርተፍኬት
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (Tin No)
- የአቅራቢነት ማስረጃ (Suppliers List)
- የሚፈለግባቸውን የመንግሥት ግብር ስለመወጣታቸው የሚገልጽ ማስረጃ፣ ፎቶ ኮፒ ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር በማያያዝ ማቅረብ አለባቸው፡፡
ተጫራቾች ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ፡- ለ10 ተከታታይ ቀናት ሰነዱን በመግዛት በ11ኛው የሥራ ቀን ጨረታው የሚዘጋና የሚከፈት ይሆናል፡፡ የጨረታ ሰነድ መግዣ ዋጋ ብር 100 (አንድ መቶ) መሆኑን እየገለጽን፤ ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዳችሁን በፖስታ በማሸግ በተጠቀሱት ቀናት ከጠዋቱ 2:30 - 8፡00 ሰዓት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ በማስገባት በጨረታው እንድትሳተፉ እንጋብዛለን፡፡
የጨረታ ሳጥኑ ከላይ በተጠቀሰው ቀን 8፡00 ሰዓት ተዘግቶ በ8፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በኢንተርፕራይዙ ዋና መ/ቤት ጎተራ አጎና ሠራዊት ሲኒማ አጠገብ ባለኬር ህንፃ /Baleker Tower 4ኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው የኦሮሚያ ምርጥ ዘር ኢንተርፕራይዝ ቢሮ ቁጥር 402 ይከፈታል። ኢንተርፕራይዙ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
የኢንተርፕራይዙ የሥራ ሰዓት፤ ከሰኞ-አርብ ጥዋት ከ2፡30-6፡30 ከሰዓት በኋላ ከ7፡30-11፡30 ሰዓት ነው።
ለበለጠ ማብራሪያ፡- ስ.ቁ 011-416 03 09/011-466-25-27 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡
የኦሮሚያ ምርጥ ዘር ኢንተርፕራይዝ
