የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ሕዳር 7/2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ጃንሜዳ ለሚያካሂደው የ43ኛው የጃንሜዳ ኢንተርናሽናል ሀገር አቋራጭ ውድድር ላይ የሚውሉ መጽሔት ለማሳተም ከዚህ በታች በተዘረዘረው ስፔስፊኬሽን መሠረት በሀገር ውስጥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሣተም ይፈልጋል።
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ሕዳር 7/2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ጃንሜዳ ለሚያካሂደው የ43ኛው የጃንሜዳ ኢንተርናሽናል ሀገር አቋራጭ ውድድር ላይ የሚውሉ መጽሔት ለማሳተም ከዚህ በታች በተዘረዘረው ስፔስፊኬሽን መሠረት በሀገር ውስጥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሣተም ይፈልጋል።
- የመጽሄት ብዛት ............................. 150
- ገጽ ብዛት .................................... 32 ከቨርን ጨምሮ
- የሽፋን ........................................ 250 ግራም
- የውስጥ ገጾች ............................... 150 ግራም
- የወረቀቱ መጠን ............................ A4
- ከለር ......................................... ባለሙሉ ቀለም
- ማት ላሚኔትድ የሆነ
- ፐርፌክት ባይንዲንግ
- ሙሉ ከቨርን ጨምሮ ከነ ዲዛይን የሚሰራ
- ከዚህ በፊት በግራፊክ ዲዛይን እና ተያያዥ ስራዎች የሰራቸውን አንድ እና ከዛ በላይ ናሙናዎች ማቅረብ አለበት።
- በአስር የስራ ቀናት ከነዲዛይኑ እና ግራፊክስ ሕትመት ሰርቶ ማስረከብ የሚችል፡፡
በዚሁ መሠረት፡-
- በጨረታው ለመወዳደር የምትፈልጉ ተጫራቾች የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸው፤ የቲን እና ቫት ተመዝጋቢ የሆኑ።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ብር 10,000.00 /አስር ሺህ ብር/ ከጨረታ ሰነድ ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፤
- ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዶቻቸውን ዋናውንና ኮፒውን በታሸገ ኤንቨሎፕ ማስታወቂያው ከወጣበት ዕስት ጀምሮ ለተከታታይ 7 የሥራ ቀናት በፌዴሬሽኑ ቢሮ ቁጥር 5 ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በሰባተኛው ቀን ከቀኑ በ8:00 ሰዓት ታሽገ በዚያው ዕለት 8:30 ሰዓት በፌዲሬሽኑ ቢሮ ቁጥር 5 (መሰብሰቢያ አዳራሽ) ይከፈታል።
- ተጫራቾች የሚወዳደሩባቸውን የመጽሔት ዋጋ ከቫት ጋር ያለውን ዋጋ እና ሳምፕል ማስቀመጥ ይጠበቅባቸዋል።
- መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡-ጉርድ ሾላ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
ሕንጻ 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 6
ለበለጠ መረጃ- 0917012504/
0116-47-95-78 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
ፋክስ 0116-45-879
ፖ.ሳ.ቁ 13336
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
