በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 ህብረት ቅድመ አንደኛ፣ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የጥገና እና እድሳት አወዳድረን ማሰራት ይፈልጋል።
የግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር 02/2018
በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 ህብረት ቅድመ አንደኛ፣ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የጥገና እና እድሳት አወዳድረን ማሰራት ስለምንፈልግ በዚህም መሰረት፡-
- ሎት1. የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች ጥገና
- ሎት2. በር፣ መስኮት፣ የመብራት መስመር ዝርጋታ፣ የግድግዳ ሶኬት እድሳት ጥገና
- ሎት3. የቧንቧ መስመር የሽንት ቤት መስመር ጥገና
- በጨረታው ለመወዳደር ፍላጎት ያላቸው በመስኩ ህጋዊ ሰነድ እና ንግድ ፍቃድ ያላቸው፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ፣ በመንግስት ግ/ን/አስ/ኤጀንሲ ድረ ገፅ ላይ በአቅራቢዎች ምዝገባ ዝርዝር የተመዘገቡ፣ የቲን እና የቫት ተመዝጋቢ የሆኑና የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ።
- ተጫራቾች በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ የሆኑና ኦርጅናልና ኮፒ በመለየት ሙሉ ሰነድ ላይ ስማቸውን ፊርማቸውን እና አድራሻ መፃፍ አለባቸው።
- ተጫራቾች ጨረታውን በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት እለት አንስቶ በተከታታይ 10 የሥራ ቀናት የማይመለስ ብር 250.00 (ሁለት መቶ ሃምሳ ብር) በመክፈል በአራዳ ክ/ከተማ ህብረት ቅድመ አንደኛ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት የቢሮ ቁጥር 5 በመምጣት የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዳቸውን በታሸገ ኤንቨሎፕ ማስታወቂያው ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ለተከታታይ 10 የሥራ ቀናት ህብረት ቅድመ አንደኛ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት በቢሮ ቁጥር 5 ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በ11ኛ ቀን ከጠዋት 4፡00 ሰዓት ታሽጎ ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት ህብረት ቅድመ አንደኛ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት ቢሮ ቁጥር 5 የሚከፈት ይሆናል።
- መስሪያ ቤቱ በሎት 2 የተጠቀሱ የጥገና ስራዎች በአካል መታችሁ ተቁዋሙ በሚያሳያቸው መሰረት አይታችሁ ዋጋ መሙላት ይጠበቅባችኋል።
- ተጫራቾች ሁሉም የጥገና ስራዎች በአካል መታችሁ ተቁዋሙ በሚያሳያቸው መሰረት አይታችሁ ዋጋ መሙላት ይጠበቅባችኋል።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ 2% በጥሬ ገንዘብ ወይም በሲፒኦ ማስያዝ አለባቸው።
- የጨረታ አሸናፊ ከተቋሙ ጋር ውል ለመዋዋል በቅድሚያ የጠቅላላ ዋጋ 10% ዋስትና ማስያዝ አለበት።
- ተጫራቾች ያሸነፉባቸውን ዘርፎች ከራሳቸው እቃ ገዝተው ጥገና የሚያከናውኑ ይሆናል።
- መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- ፒያሳ ከመብራት ኃይል ወደ እሪበከንቱ በሚወስደው መንገድ ጎጀብ ጥርስ ህክምና ጎን
ለበለጠ ማብራሪያና ጥያቄ
ስልክ ቁጥር 09-12-85-03-39/09-11-38-31-11
በአራዳ ክ/ከተማ ህብረት ቅድመ አንደኛ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት
