የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት ለ2018 በጀት ዓመት ለሠራተኞች የደንብ ልብስ አገልግሎት የሚውሉ ብትን ጨርቅ፣ የወንድ ጫማ፣ የሴት ጫማ፣ ሴፍቲ ጫማ፣ ሽሚዝ፣ የዝናብ ልብስ፣ የሱፍ ካፖርት፣ የጽዳት ሽርጥ፣ ቱታ እና ልዩ ልዩ የደንብ ልብሶችን በግለጽ የጨረታ ማስታወቂያ ከአቅራቢ ድርጅቶች አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ የጨረታ መለያ ቁጥር ኢሎአ /001/2018
የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት ለ2018 በጀት ዓመት ለሠራተኞች የደንብ ልብስ አገልግሎት የሚውሉ ብትን ጨርቅ፣ የወንድ ጫማ፣ የሴት ጫማ፣ ሴፍቲ ጫማ፣ ሽሚዝ፣ የዝናብ ልብስ፣ የሱፍ ካፖርት፣ የጽዳት ሽርጥ፣ ቱታ እና ልዩ ልዩ የደንብ ልብሶችን በግለጽ የጨረታ ማስታወቂያ ከአቅራቢ ድርጅቶች አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ስሰዚህም በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ድርጅቶች ሁሉ ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ላይታትሞ ከመጣበት ዕለት ጀምሮ እስከ ህዳር 12 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ ለዚህ ሥራ የተዘጋጀውን የጨረታ ሠነድ የማይመለስ ብር 200 (ሁለት መቶ ብር) በመከፈልና በመግዛት መወዳደር ይችላሉ፡፡
ተጫራቾች በኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት ስም የጨረታ ማስከበሪያ ብር 250,000 (ሁለት መቶ ሃምሳ ሺህ ብር) በሲፒኦ፣ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንከ ጋራንቲ ዋናውን ማስረጃ ማያያዝ አለባቸው፡፡ ተጫራቾች በስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ጽ/ቤት ውስጥ የተደራጁ ህጋዊ ጥቃቅንና አነስተኛ ማህበራት በጨረታው ለመወዳደር የጨረታ ማስከበሪያ ማስያዝ አለባቸው፤ ከአደራጃቸው ተቋም የሚያቀርቡት የድጋፍ ደብዳቤ ውስጥ መካተት ያለባቸው ሁኔታዎች የሚወዳደሩበትን ተቋም ስም፣ የሚወዳደርበትን የግዥ ዓይነት፣ የጨረታ ቁጥር እና የጨረታ ማስከበሪያውን የገንዘብ መጠን በግልጽ በአሃዝና በፊደል የተፃፈ የድጋፍ ደብዳቤ ማቅረብ አለባቸው::
ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዶችን የቴከኒካልና ፋይናንሻል ሰነዶችን የያዘ አንድ ዋና እና አንድ ቅጂ ለየብቻው በፖስታ በማድረግና በፅሁፍ በመለየት የታደሰ የንግድ ስራ ፈቃድ፣ የንግድ ምዝገባ ምስከር ወረቀት፣ የተጨማሪ ከሴት ታከስ የምስከር ወረቀት፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር የምስከርወረቀት፣ በጨረታ ለመሳተፍ የሚያገለግል ከሪላንስ፣ የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ሬጀንሲ በአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡበትን የምስክር ወረቀት፣ የማጭበርበር ድርጊት ላለመፈፀም ቃል ሚገባበት ቅፅ ሞልታችሁ ማህተምና ፊርማ አድርጋችሁ የመጫረቻ ለነዶቻችሁን አሟልታችሁ በማቅረብና የጨረታ ማስከበሪያውን በታሸገ ፖስታ በማድረግ እስከ ህዳር 12 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ስዓት ድረስ ለዚሁ ሥራ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ገቢ ማድረግ አለባቸው::
ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በሚገኙበት ህዳር 12 ቀን 2018 ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት ፒያሳ ጣይቱ ሆቴል አጠገብ በሚገኘው የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት ዋና መ/ቤት ይከፈታል። አገልግሎቱ ስለጨረታው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታን በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 011-126-78-16 ደውሎ መረዳት ይቻላል፡፡
የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት
