አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ በጨረታ ቁጥር ኢ.ሚ.ኔ.በ.ግ.ጨ. 006/2018 ዓ.ም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ነገሮች በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
በጨረታ ቁጥር ኢ.ሚ.ኔ.በ.ግ.ጨ. 006/2018 ዓ.ም በግልጽ ጨረታ ተጫራቾችን አወዳድሮ ለመግዛት የሚፈልግ
በመሆኑ በጨረታ ለመሳተፍ የምትፈልጉ፡-
· ሎት 1. በየሳምንቱ የሚወጣ የጋዜጣ ኅትመት አገልግሎት ግዥ
· ሎት 2. የሬዲዮና የቴሌቪዥን ስቱዲዮ እኮስቲክስ ሥራ ግዥ
· ሎት 3. የጀኔሬተር መለዋወጫ እቃዎች ግዥ (በድጋሚ የወጣ)
· ሎት 4. ማይክ ሎጎ (በድጋሚ የወጣ)
· ሎት 5. ጊንባል ግዥ (በድጋሚ የወጣ)
· ሎት 6. የሬዲዮ የሲትኮም የአማርኛ ድራማ አገልግሎት ግዥ (በድጋሚ የወጣ)
· ሎት 7. የአፋን ኦሮሞ የቴሌቪዥን ድራማ (በድጋሚ የወጣ)
· ሎት 8. የልብስ ኪራይ አገልግሎት ግዥ
· ለሎት 9. የስፖርት ትጥቅ
· ሎት 10. የተፈጥሮ የማዕድን ውሃ (በድጋሚ የወጣ)
· ሎት 11. ስዊች 48ፖርት
በጨረታ ቁጥር አ.ሚ.ኔ.በ.ግ.ጨ. 006/2018ዓ.ም በግልጽ ጨረታ ተጫራቾችን አወዳድሮ ለመግዛት የሚፈልግ
በመሆኑ በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ ፡-
1. በዘርፉ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉ፡፡
2. የተጨማሪ እሴት ታክስ እና የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር የምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችሉና በግዥ አቅራቢነት የተመዘገቡ፣
3. ተጫራቾች በሚያቀርቡት እያንዳንዱ ሰነድ እና በፖስታ ላይ የድርጅቱን ማህተምና ፊርማቸውን ማኖር ይጠበቅባቸዋል፡፡
4. ተጫራቾች ለሚያቀርቡት አጠቃላይ ዋጋ ሎት1. =50,000 ብር ለሎት2. =300,000 ብር፣ ለሎት3. =200,000ብር ለሎት4 =30,000 ብር፣ ለሎት5= 200,000 ብር፣ ለሎት6 =50,000 ብር፣ ለሎት7 =50,000 ብር፣ ለሎት8 =20,000 ብር፣ ለሎት9 =75,000 ብር፣ ለሎት 10 =20,000 ብር እና ለሎት 11 =200,000 ብር በባንክ በተረጋገጠ ሲፒአ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንከ ዋስትና ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
5. ተጫራቾች የጨረታውን ዝርዝር የሚያሳይ የጨረታ ሰነድ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 10 የሥራ ቀናት ውስጥ አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ቢሮ ቁጥር 6 ለሰነዱ ክፍያ በመክፍል ዘወትር በሥራ ሰዓት 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 28 ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡
6. ጨረታው በ11ኛው ቀን ከረፋዱ 4፡00 ተዘግቶ በዚሁ ቀን በረፋዱ 4፡30 ተጫራቾች ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ 8ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 108 ይከፈታል፡፡ ሆኖም ግን የተጫራቾች አለመገኘት ጨረታውን ለመክፈት አያግደውም። የመክፈቻው ዕለት በዓል/ዕረፍት ቀን ከሆነ በቀጣዩ የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ተዘግቶ ይከፈታል፡፡
7. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሃሳባቸውን ዋናውንና ኮፒውን/ቴክኒካል ኦሪጅናልና ኮፒ፣ ፋይናንሻል ኦሪጂናልና ኮፒ/በተለያየ ፖስታ በማሸግ በዚሁ ተብሎ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይጠበቅባቸዋል፡፡
8. በአንዱ ተጫራች ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ የተከለከለ ነው።
9. በጨረታ ያሸነፈ ተጫራች ከመ/ቤታችን ጋር ጨረታውን እንዳሸነፈ ካወቀበት ጊዜ አንስቶ በ15 ቀናት ውስጥ በሲፒኦ የጠቅላላ ዋጋውን 10% በማስያዝ ውል መዋዋል ይኖርበታል፡፡
10. ተቋሙ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፈል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ 5 ኪሎ ቅድስት ማሪያም ቤ/ክርስቲያን ከማህበረ ቅዱሳን ጀርባ ያለው ለበለጠ መረጃ፡- ስልክ ቁጥር፡- 0111116382 መደወል ይችላሉ፡፡
አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ
