በአዲስ ከተማ ጤና ጣቢያ የ2018 በጀት አመት በአዲስ ዘመን በጋዜጣ ባወጣው ግልጽ ጨረታ ለተጫራቾች የተዘጋጀ አገልግሎት ግዥ lot 1ቋሚ እቃ አወዳድሮ ለመግዛት በጨረታ ይፈልጋል።
የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር፡-003
በአዲስ ከተማ ጤና ጣቢያ የ2018 በጀት አመት በአዲስ ዘመን በጋዜጣ ባወጣው ግልጽ ጨረታ ለተጫራቾች የተዘጋጀ አገልግሎት ግዥ lot 1ቋሚ እቃ አወዳድሮ ለመግዛት በጨረታ ይፈልጋል።
ስለዚህ በመስኩ የተሰማራችሁ አቅራቢዎች
- በዘመኑ የታደሰ ንግድ ፈቃድ
- የግብር ከፍይ መለያ ቁጥር
- በአቅራቢዎች ዝርዝር የተመዘገበ
- የተጨማሪ እሴት ታክስ /vat/ ሰርተፍኬት ወይም TOT 2%
- ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ግዜ ጀምሮ ተመላሽ የሚሆን የጨረታ ማስከበሪያ ሎት1 ቋሚ እቃዎች ሲፒኦ 2% (10,000)) ብር ብቻ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ከጨረታ ሰነድ ጋር በማያያዝ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ለዚሁ ጨረታ የተዘጋጀውን ዝርዝር ጉዳዮች እና የተጫራቾችን መመሪያ የያዘ ሰነድ ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የማይመለስ የጨረታ ሰነድ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ በመግዛት መውሰድ ይችላሉ።
- ጨረታው መጀመሪያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10 የስራ ቀናት ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ እስከ 11፡30 ድረስ ብቻ ማስገባት ይኖርባቸዋል። ጨረታው የሚዘጋው በ 11ኛው ቀን ከጠዋቱ 2፡30 ታሽጎ 3፡00 ላይ ተጫራቾች ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
- አሸናፊው ድርጅት ውል በተፈራረመበት በ15 ቀን ውስጥ እታውን ያቀርባል።
- አሸናፊ ሆኖ የተመረጠው ድርጅት በአካል በመቅረብ ስራውን ማከናወን አለበት
- ጨረታው ከተከፈተ ተጫራቾች ባቀረቡት የመወዳደሪያ ሀሳብ ላይ ለውጥ ወይም ማሻሻያ ማድረግ ወይም ከጨረታው እራሳቸውን ማግለል አይችሉም።
- ተጫራቾች የዋጋ ዝርዝራቸውን በገዙት የጨረታ ሰነድ ላይ ብቻ ሞልተው እና በእያንዳንዱ ላይ ገጽ ላይ ማህተም በማድረግ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- የጨረታው አሸናፊ የሆነው ግለሰብም ሆነ ድርጅት ውል በሚያዝበት ወቅት ያሸነፈበትን የሽያጭ ጠቅላላ ዋጋ 10% የውል ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዛዝ (cpo) ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች በገዙት ሰነድ መሰረት የሚወዳደሩበትን ዋጋ 15% vat ያካተተ መሆኑን ወይም አለመሆኑን መጠቀስ ይኖርበታል ካልተጠቀሰ እንደተካተተ ተደርጎ ይወሰዳል።
- ኦርጂናል ሰነድ ከ ሙሉ ሰነድ ጋር እና ኮፒውን ሰነድ ለየብቻ ተደርጎ በማያያዝ ማስገባት ይኖርባቸዋል እንዲሁም የድርጅቱ ማህተብ እያንዳንዱ ሰነዶች ላይ መደረግ አለበት።
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ ለሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ማንኛውም ተጫራች መደበኛ የጨረታ ሰነዱን የሚሞሉ ክፍሎችን በአግባቡ ሞልቶ ተመላሽ ያላደረገ አቅራቢ ቅድመ ምርመራ ጨረታ ላይ ውድቅ ይደረጋል።
- የጥቃቅን አነስተኛ የተደራጀ ልዩ አስተያየት የሚደረገው በሚያመርቱት ምርት ብቻ ሆኖ ከተደራጁበት ተቋም በሚያቀርቡት ደብዳቤ ይሆናል።
ተጨማሪ መረጃ
የጨረታ ሰነድ የሚገኝበት ቦታ አ/ከ/ክ/ከ/ጤና ጣቢያ መሳለሚያ እህል በረንዳ ከእሳት አደጋ በስተጀርባ በሚገኘው ግዥ ቢሮ ቁጥር 5 በአካል በመቅረብ መውሰድ ይችላሉ ።
የአዲስ ከተማ ጤና ጣቢያ
