የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት በ2018 በጀት ዓመት አገልግሎት ላይ የሚውሉ የጽሕፈት መሳሪያዎችና የጽዳት መገልገያ ዕቃዎችን ከአቅራቢ ድርጅቶች በግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ ውድድር መሠረት ሎት 1፡- የጽሕፈት መሳሪያ ዕቃዎች እና ሎት 2፡- የጽዳት መገልገያ ዕቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ መስያ ቁጥር ኢሎአ/003/2018
የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት በ2018 በጀት ዓመት አገልግሎት ላይ የሚውሉ የጽሕፈት መሳሪያዎችና የጽዳት መገልገያ ዕቃዎችን ከአቅራቢ ድርጅቶች በግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ ውድድር መሠረት
ሎት 1፡- የጽሕፈት መሳሪያ ዕቃዎች እና
ሎት 2፡- የጽዳት መገልገያ ዕቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለዚህም በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ድርጅቶች ሁሉ ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ላይታትሞ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ እስከ ህዳር 24 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ በዚህ ሥራ የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 200 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈልና በመግዛት መወዳደር ይችላሉ፡፡
ተጫራቶች ሎት-1 ላይ የሚወዳደሩ ድርጅቶች ለጨረታ ማስከበሪያ ማስያዝ ያለባቸው ብር150,000.00 (እንድ መቶ ሃምሳ ሺህ ብር) እንዲሁም ሎት-2 ላይ የሚወዳደሩ ድርጅቶች የጨረታ ማስከበሪያ ማስያዝ ያለባቸው ብር 130,000.00 (አንድ መቶ ሰላሳ ሺህ ብር) በሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ጋራንቲ በማሲያዝ ዋናው ሰነድ ማያያዝ አለባቸው:: ተጫራቾች በሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ጽ/ቤት ውስጥ የተደራጁ ህጋዊ ጥቃቅንና አነስተኛ ማህበራት በጨረታው ለመወዳደር የጨረታ ማስከበሪያ ማስያዝ ያለባቸው ከአደራጃቸው ተቋም የሚያቀርቡት የድጋፍ ደብዳቤ ውስጥ መካተት ያለባቸው ቅድመ ሁኔታዎች ጨረታ የሚወዳደሩበት ተቋም ስም፣ የግዥ ዓይነት፣ የጨረታ መለያ ቁጥርና የጨረታ ማስከበሪያውን የገንዘብ መጠን በግልጽ በአሃዝና በፊደል የተፃፈ የድጋፍ ደብዳቤ ማቅረብ አለባቸው፡፡
ተጫራቾች የቴከኒከና ፋይናንሻል ሰነዶችን የያዘ አንድ ዋና እና አንድ ቅጂ ለየብቻው በፖስታ በማድረግና በፅሁፍ በመለየት የታደሰ የንግድ ሥራ ፈቃድ፣ የንግድ ምዝገባ ምስከር ወረቀት፣ የተጨማሪ እሴት ታከስ የምስክር ወረቀት፣
የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር የምስከር ወረቀት፣ ጨረታ ለመሳተፍ የሚያገለግል ኪሊራንስ፣ በመንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ በአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡበት የምስክር ወረቀት፣ የማጭበርበር ድርጊት ላለመፈፀም ቃል የሚገባበት ቅፅ ሞልተው ከመጫረቻ ሠነዶቻቸውና የጨረታ ማስከበሪያውን በታሸገ ፖስታ በማድረግ እስከ ህዳር 24 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ ለዚሁ ሥራ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሀጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ህዳር 24 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት ፒያሳ ጣይቱ ሆቴል አጠገብ በሚገኘው የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት ዋና መ/ቤት ይከፈታል፡፡
አገልግሎቱ ስለጨረታው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 011-126-78-16 ደውሎ መረዳት ይቻላል፡፡
የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት
