በአሮሚያ ግብርና ኅብረት ሥራ ማኅበራት ፌዴሬሽን ኃ/የተወሰነ የአሰላ ብቅል ፋብሪካ የተለያዩ ያገለገሉ ተሽከርካሪዎችን ባሉበት ሁኔታ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
በድጋሚ የወጣ የተለያዩ ያገለገሉ ተሽከርካሪዎች ሽያጭ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር OAC, AMF/MS/01/2018
በአሮሚያ ግብርና ኅብረት ሥራ ማኅበራት ፌዴሬሽን ኃ/የተወሰነ የአሰላ ብቅል ፋብሪካ የተለያዩ ያገለገሉ ተሽከርካሪዎችን ባሉበት ሁኔታ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
ስለሆነም በጨረታው ለመወዳደር ፍላጎትና አቅም ያላቸው ተጫራቶች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ማሟላት አለባቸው።
- ተጫራቾች የዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /Tin No./ተመዝጋቢ ስለመሆናቸው ሕጋዊ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ መሆን ይኖርባቸዋል።
- የጨረታ ሰነዱን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ) በፋብሪካችን አካውንት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000257808697 ወይም በአሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ 1000043405229 ገቢ በማድረግ ዘወትር በሥራ ሰዓት ከሰኞ እስከ ዓርብ ጠዋት 2፡00-6፡00 ከሰዓት በኋላ ከ7፡00-10፡00 ሰዓት ቅዳሜ ጠዋት 2፡00- 6:00 ሰዓት ድረስ አሰላ-ቁለምሳ በሚገኘው ፋብሪካችን ቢሮ ቁጥር 051 ወይንም አዲስ አበባ በሚገኘው ዋና መ/ቤት ከጀርመን አደባባይ ወደ ሚካኤል አደባባይ በሚወሰደው መንገድ ላይ ሚካኤል ቤ/ክርስቲያን አጠገብ በሚገኘው የኦሮሚያ ግብርና ኅብረት ሥራ ማኅበራት ፌዴሬሽን ሕንፃ ስድስተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 6 ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ተሽከርካሪ ጠቅላላ ዋጋ 5% የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በባንክ በተመሰከረለት ሲፒኦ /CPO/ ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ታኅሳስ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ድረስ በአየር ላይ ክፍት ሆኖ ይቆያል።
- ተጫራቾች በኤንቨሎፕ የታሸገ የጨረታ ሰነዳቸውን በአሰላ ብቅል ፋብሪካ ቢሮ ቁጥር 051 በተቀመጠው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።
- ጨረታው በዕለቱ ታኅሳስ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ በ8፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዕለቱ በ8፡15 ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት አሰላ /ቁሉምሳ/ በሚገኘው የፋብሪካችን የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል።
- ተሽከርካሪዎቹን ከላይ በተራ ቁጥር 2 በተለገጹት የሥራ ቀናት አሰላ ቁለምሳ በሚገኘው የፋብሪካው ቅጥር ግቢ ማንነታቸውን የሚገልጽ መታወቂያ በመያዝ በአካል በመገኘት ማየት ይችላሉ።
- የጨረታ ሳጥኑ ከታሸገ በኋላ ጨረታ ሰነዳቸውን የሚያቀርቡ ተጫራቾች ተቀባይነት አይኖራቸውም።
- ፋብሪካው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ ማብራሪያ
ስልክ ቁጥር፡- 022 331 52 66 ወይም 022 331 81 97 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል።
በኦሮሚያ ግብርና ኀብረት ሥራ ማኅበራት ፌዴሬሽን ኃ/የተወሰነ የአሰላ ብቅል ፋብሪካ
