የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የሚያገለግል A5 ስቲከር (A5 adhesive Sticker) ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የስቲከር ግዥ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር NEBE/NCB/05/2018
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የሚያገለግል A5 ስቲከር (A5 adhesive Sticker) ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
1. በጨረታው ለመወዳደር የሚፈልጉ ተጫራቾች ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ጨረታው መዝጊያ ቀን ታህሳስ 01 ቀን 2018 ዒ.ም ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 6፡ 30 እና ከ7፡30 እስከ 11፡30 ሰዓት ድረስ ባሉት የስራ ቀናት የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 200.00/ሁለት መቶ ብር/በመክፈል ከቦርዱ ግዥ ስራ ክፍል ቢሮ ቁጥር 107 ማግኘት ይችላሉ።
2. ተጫራቾች በዘርፉ የታደሰ የንግድ ስራ ፍቃድ፣የተጨማሪ እሴት ታከስና የዘመኑ ግብር የከፈሉ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ምዝገባ ምስክር ወረቀት (ታከስ ክሊራንስ) እንዲሁም በመንግሥት የኤሌክትሮኒከስ ግዥ ድህረ-ገጽ የአቅራቢነት ዝርዝርየተመዘገቡ ስለመሆኑ የሚያሳይ ማስረጃ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
3. የጨረታ ሰነዱን ከቦርዱ ዋና መስሪያ ቤት የግዥ አስተዳደር የስራ ክፍል በመውሰድ ሞልተው አግባብ ባለው አካል በመፈረም ለዚሁ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
4. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን የቴከኒክና የዋጋ ሰነዳቸውን ኦርጅናልና ኮፒ በማሸግ ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ እስከ ጨረታው መዝጊያ ሰዓት ድረስ ውስጥ እስከ ጨረታው መዝጊያ ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
5. ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያነት ብር 50,000.00 (ሃምሳ ሺህ ብር) በባንከ የተረጋገጠ የክፍያ ማዘዣ (ሲፒኦ) ወይም በቅድመ ሁኔታ ላይ ባልተመሰረተ የባንከ ዋስትና ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
6. ጨረታው ታህሳስ 01 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዕለቱ ከቀኑ 8፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
7. ቦርዱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
8. ተጨማሪ ማብራርያ ካስፈለገ በአካል ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ አድራሻ ቦሌ መንገድ ፍላሚንጎ ሬስቶራንት ገባ ብሎ ካለው ዋና መ/ ቤት በመቅረብ መጠየቅ ይችላሉ፡፡
አድራሻችን፡-ቦሌ ፍላሚንጎ ካፌ ገባ ብሎ
ስልክ ቁጥር፡ +251115153468
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
