በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በቡኖ በደሌ ዞን ገቺ ወረዳ ገ/ጽ/ቤት በወረዳው ለሚገኘው የወረዳው መንገዶች እና ሎጅስቲክ ጽ/ቤት በወረዳው ውስጥ የሚገኙትን መንገዶች ህጋዊ የሆነትን ድርጅቶች በግለጽ ጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል። ስለዚህ ለስራው የሚያስፈልጉ የማሽን አይነት D8R ዶዘር እና እስካባተር (CAT)፣ ዶሰን (Doesne) ለመከራየት ጠጠር (Material) ለማምረት ለመጫን እና ግሬደር CAI 140፤ ዳምፕትራክ፤ ሻወርትራክ 20 ሺህ ሊትር በላይ ሩሎ ባለ 12 ቶን በመከራየት የገጠር መንገድ መስራት ይፈልጋል፡፡
ለአንደኛ ጊዜ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር 04
በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በቡኖ በደሌ ዞን ገቺ ወረዳ ገ/ጽ/ቤት በወረዳው ለሚገኘው የወረዳው መንገዶች እና ሎጅስቲክ ጽ/ቤት በወረዳው ውስጥ የሚገኙትን መንገዶች ህጋዊ የሆነትን ድርጅቶች በግለጽ ጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል። ስለዚህ ለስራው የሚያስፈልጉ የማሽን አይነት D8R ዶዘር እና እስካባተር (CAT)፣ ዶሰን (Doesne) ለመከራየት ጠጠር (Material) ለማምረት ለመጫን እና ግሬደር CAI 140፤ ዳምፕትራክ፤ ሻወርትራክ 20 ሺህ ሊትር በላይ ሩሎ ባለ 12 ቶን በመከራየት የገጠር መንገድ መስራት ይፈልጋል፡፡
ስለዚህ ተጫራቾች፡-
- ተጫራቾች ተወዳዳሪዎች /ኩባንያ ማሽን ለማከራየት የስራ ፍቃድ ያላቸውና ማቅረብ የሚችሉ።
- ተጫራቾች ተወዳዳሪዎች በጨረታው ለመወዳደር የዘመኑ ግብር የከፈሉ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ መረጃ ከሀገር ውስጥ ገቢ መ/ቤት ወይም ከጉሙሩክ ባለስልጣን ወይም ከፈዴራል ሀገር ውስጥ ገቢ መ/ቤት ማቅረብ አለባቸው እንዲሁም የተጨማሪ እሴት ታክስ VAT / 15% ተመዝጋቢ መሆናቸው የሚገልጽ ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው።
- ተፈላጊ የማሽን ዓይነት ከላይ የተገለጹት ሆኖ ባለቤት መሆናቸውን ወይም ለመከራየታቸው ለእያንዳንዱ ማሽን ማስረጃ የሚያቀርብ መሆን ይጠበቅበታል፡፡
- ተጫራቾች ተወዳዳሪዎች ድርጅት የስራ ልምድ ያለውን ኦፕሬተር ማቅረብ የሚችልና ኦፕሬተሩ ችግር ከፈጠረ መቀየር የሚችል መሆን አለበት።
- ተጫራቾች በስራ ላይ የሚያጋጥሙ ችግሮች ካሉ የማሽኑን ጥገና ወጪ በራሳቸው ለመሸፈን ዝግጁ የሆኑ፡፡
- መ/ቤቱ ለማሰራት ካወዳደረው መንገዶች ውስጥ 20% ጨምሮ የማሰራት ወይም ማሽኖችን የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ተወዳዳሪ አሸናፊ ማሽኖችን ለስራው የሚያስፈልጉ ነዳጅ፣ አይነት፣ ግራሶ እና ሌሎችንም ወጪዎች ራሳቸው ለመሸፈን ፈቃደኛ የሆኑ።
- ተጫራቾች ማሸኑን ጭነው ማቅረብና ከሳይት ወደ ሳይት በራሳቸው ወጪ ማጓጓዝ የሚችሉ መሆን አላባቸው።
- ተጫራቾች የውል ስምምነት ከፈጸሙ መሥሪያ ቤቱ በፈለገበት ቀናት ውስጥ ማሸኑን ወደ ስራ ቦታ ለማስገባት ዝግጁ የሆነ።
- ተጫራቾች ካሁን በፊት ከላይ በተዘረዘሩ ማሽኖች ተወዳድረው አሸንፈው ከሰሩት መ/ቤት የተሰጣቸው የስራ ጥራት የምስክር ወረቀት ደብዳቤ /ቢያንስ ከ (1) መ/ቤት ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች ጨረታውን ማስከበርያ ገንዘብ ብር 100,000.00 /አንድ መቶ ሺህ ብር/ በጥሬ ገንዘብ ወይም በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ጨረታው ከመከፈቱ በፊት ከጨረታ ሰነድ ጋር አያይዞ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቶች ጨረታውን ማሸነፋቸው ከተገለጸላቸው ቀን ጀምሮ በ10 ቀናት ውስጥ የውል ስምምነት ለመፈጸም ዝግጁ የሆነ።
- ተጫራቾች የሚያቀርቡት ማሽን 2012 እ.አ.አ እና ከዛ በላይ የተመረቱ በቂ ፕርፎረማንስ ሊኖረው የሚገባ መሆን አለበት ። ከሚጠበቀው /Standard/ በታች ከሆነ በሌላ ለመተካት ፈቃደኛ የሆነ መሆን አለበት።
- ተጫራቾች ጨረታውን በሁለት ኮፒ በሰም በማሸግ የሚመለከተውን የድርጅቱን ሃላፊ ማስፈረምና ህጋዊ ማህተም አድርገውበት ማቅረብ አለባቸው። ሆኖም የጨረታ ሳጥን ከተዘጋ በኋላ የሚቀርብ ሰነድ ተቀባይነት የላቸውም።
- ተጫራቾች ጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት አንስቶ ለተከታታይ 21 የስራ ቀናት የጨረታውን ሰነድ ከገቺ ወረዳ ገቢዎች ባለስልጣን ጽ/ቤት የማይመለስ ብር 1000.00 / አንድ ሺህ ብር ብቻ በመክፈል መግዛት ይችላሉ፡፡ ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በ21ኛው በስራ ቀን ከ19/3 እስከ 17/4/2018 የጨረታው ሣጥን በዚሁ ቀን በ8፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ቀን በበ8፡30 ሰዓት ተጫራቾች ባሉበት በወረዳ ፕሮጀከት ኮሚቴ ይከፈታል ።
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ ስልክ ቁጥር 0945651357,0926029878 ሁሌም በሥራ ሰዓት መደወል ይቻላል፡፡
በቡኖ በደሌ ዞን የገቺ ወረዳ ገንዘብ ፅ/ቤት
