የአዳማ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በአፈፃፀም ክስ ክርክር ጉዳይ አስመልክቶ በአዳማ ከተማ ወረዳ ጎሮ ውስጥ የሚገኘውን ጨረቃ መኖሪያ ቤት በጨረታ እንዲሸጥ ፍ/ቤቱ አዟል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የፍርድ ባለ መብት አቶ ገለቶ ሃጂ እና የፍርድ ባለ እዳ 1. ሽጉጢ ድንቁ 2 መገርሳ ተርባባ መካከል ያለውን የአፈፃፀም ክርክር በተመለከተ በአዳማ ከተማ ወረዳ ጎሮ ውስጥ የሚገኘውን ጨረቃ መኖሪያ ቤት የቦታው ስፋት 105 ሜ የሆነ አዋሳኙ በምስራቅ ዘውዱ ማሙዬ በምዕራብ ሚጡ አብዶ በሰሜን የግል መኖሪያ ቤት እና በደቡብ መንገድ የሆነ የጨረታው መነሻ ዋጋ ብር 508,207.37 (አምስት መቶ ስምንት ሺህ ሁለት መቶ ሰባት ብር ከ37/100) በቀን 20/04/2018 ጠዋት ከ3፡00 ሰዓት እስከ 6፡30 ግልጽ በሆነ ጨረታ ስለሚሸጥ ተወዳድሮ መግዛት የሚፈልግ ሰው ካለ ቤቱ የሚገኝበት ቦታ አዳማ ከተማ ቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ ጎሮ ለአፈፃፀም ምክንያት የሆነው ቤት መነሻ ግምት 1/4 አስይዞ ሲፒኦውን ይዞ ጨረታው በሚካሄድበት ቀን በተባለው ቀን እና ሰዓት እዛ ቦታ ላይ በመገኘት ተወዳድሮ መግዛት የሚችል መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
የአዳማ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት
