ብርሃን ባንክ አ.ማ ከዚህ በታች የተገለፀዉን ያገለገለ ቶዮታ አዉቶሞቢል አሶሳ ከተማ ላይ ባለበት ሁኔታ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
ያገለገለ ተሽከርካሪ ሽያጭ ጨረታ ማስታወቂያ
ጨረታ ቁ. ብ/ባ/ፕ/ማ-04/18
ብርሃን ባንክ አ.ማ ከዚህ በታች የተገለፀዉን ያገለገለ ቶዮታ አዉቶሞቢል አሶሳ ከተማ ላይ ባለበት ሁኔታ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
|
ተ.ቁ |
ለጨረታ የቀረበው ያገለገለ ተሸከርካሪ |
የተመረቱበት ዓ/ም |
ብዛት |
|
1 |
ያገለገለ ቶዮታ አዉቶሞቢል |
2005 ዓ/ም |
01 |
- ተጫራቾች ለጨረታ የቀረበዉን አዉቶሞቢል አሶሳ ከተማ ባምቡ ፓራዳይዝ ሆቴል አጠገብ በሚገኘዉ ብርሃን ባንክ ቅርንጫፍ በመገኘት ማየት ይችላሉ።
- ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ፣ ተጫራቾች የማይመለስ ብር 300.00 (ሶስት መቶ ብር) በማንኛዉም የብርሃን ባንክ ቅርንጫፍ ክፍያ ፈፅመዉ ደረሰኙን በማቅረብ፣ አሶሳ ከተማ ባምቡ ፓራዳይዝ ሆቴል አጠገብ ከሚገኘዉ ብርሃን ባንክ ቅርንጫፍ እና በተጨማሪም የባንኩ ዋና መስሪያ ቤት ከሚገኝበት ቦሌ፣ ቀድሞ ብራስ ሆስፒታል ከነበረበት ቦታ ፊት ለፊት ከሚገኘዉ ወመሳድኮ ህንፃ 2+ ፎቅ ፕሮፐርቲ እና ሎጂስቲክስ አስተዳደር መምሪያ ቢሮ በመገኘት ለጨረታዉ የተዘጋጀዉን ሰነድ መግዛት ይችላሉ።
- ተጫራቾች በጨረታ ሰነዱ ላይ በተገለፀዉ መሰረት ለአዉቶሞቢሉ የተጠቀሰዉን የጨረታ ማስከበሪያ ገንዘብ በብርሃን ባንክ ስም የተዘጋጀ C.P.O. ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች አወቶሞቢሉን ሊገዙ የሚችሉበትን ዋጋ ከጨረታ ሰነዱ ጋር ተዘጋጅቶ በቀረበዉ የዋጋ ማቅረቢያ ፎርም ላይ በመሙላት ከጨረታ ማስከበሪያ C.P.O ጋር አያይዘዉ በታሸገ ኤንቬሎፕ ዘወትር በሥራ ሰዓት እስከ ታህሳስ 15 ቀን 2018 ዓ/ም. ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ድረስ አሶሳ ከተማ ባምቡ ፓራዳይዝ ሆቴል አጠገብ በሚገኘዉ ብርሃን ባንክ ቅርንጫፍ በመገኘት ለዚሁ በተዘጋጀ ሳጥን ማስገባት ይችላሉ።
- ጨረታዉ ታህሳስ 15 ቀን 2018 ዓ/ም. ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት አሶሳ ከተማ ብርሃን ባንክ ቅርንጫፍ ይከፈታል።
- ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ ጨረታዉ በሚከፈትበት ቀንና ሰዓት ባይገኙ በሌሉበት ይከፈታል።
- የጨረታው አሸናፊ አሸናፊነቱ በደብዳቤ ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ ያሸነፈበትን ጠቅላላ ዋጋ በ10 (አስር) ቀናት ውስጥ አጠቃሎ በመክፈል አዉቶሞቢሉን ማንሳት ይኖርባቸዋል። ይህን ሳያደርጉ ቢቀር ለጨረታ ማስከበሪያ ያሲያዙት ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ይደረጋል።
- የጨረታው አሸናፊ ከስም ማዛወሪያ ጋር የተያያዙ ወጪዎችን በራሱ ይሸፍናል።
- ጨረታዉ ከመካሄዱ በፊትም ሆነ ከተካሄደ በኋላ ባንኩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን የመሰረዝ መብት አለው
- ተጨማሪ መረጃ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 0917856533 /057-7751535/0577751353 / 0116631729 ማግኘት ይችላሉ።
