በደ/ም/ኢት/ህ/ክ/መ/ በካፋ ዞን የካፋ ሁለ/ህ/ሰራ ዩኒየን በ2018 በጀት ዓመት ለዞኑ አርሶአደሮች የሚያሰራጨውን የአፈር ማዳበሪያ ለሚያጓጉዙ የጭነት መኪና ያላቸውን ትራንስፖርተሮች አጫርቶ ለማስጫን ጨረታ አውጥቷል።
የጨረታ ማስታወቂያ
በደ/ም/ኢት/ህ/ክ/መ/ በካፋ ዞን የካፋ ሁለ/ህ/ሰራ ዩኒየን በ2018 በጀት ዓመት ለዞኑ አርሶአደሮች የሚያሰራጨውን የአፈር ማዳበሪያ ለሚያጓጉዙ የጭነት መኪና ያላቸውን ትራንስፖርተሮች አጫርቶ ለማስጫን ጨረታ አውጥቷል። ጨረታው በጋዜጣ ላይ ይፋ ከተደረገበት ቀን ጀምሮ ለ15 ቀናት የሚቆይ ሲሆን፤ በ16ኛው ቀን ከቀኑ 8:00 ሰዓት ላይ ታሽጎ በ8:30 ላይ ተጫራቾች ህጋዊ ወኪሎች በተገኙበት ይከፈታል። ጨረታው ተጫራቾች ባይገኙም ይከፈታል።
በዚሁ መሠረት በጨረታው መሳተፍ የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች አሟልተው መገኘት አለባቸው።
- በመስኩ የዘመኑን ንግድ ስራ ፈቃድ ያሳደሱበትን መረጃ ፣
- የግብር ከፋይነት ምዝገባ ምስክር ወረቀት እና የአቅራቢነት ምዝገባ ምስክር ወረቀት የማይመለስ ኮፒ ማቅረብ አለባቸው
- የባለቤትነት ማረጋገጫ ሊብሬ ውክልና መያያዝ አለባቸው።
- ተጫራቹ በቀጥተኛ ስራ መስክ ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ በመንግስት ግዥ ላይ በመሳተፍ በገቡት ውል መሰረት ስለማቅረባቸው የመልካም ስራ አፈጻጸም ማረጋገጫ ማቅረብ አለባቸው።
- የሚጫረቱት መኪና የመጫን አቅሙ 200 ኩ/ል እና ከዚያ በላይ መሆን አለበት፡፡
- ተጫራቾች ዋጋ የተሞላበትን ኦርጅናልና አንድ ኮፒ በመለየት ፊርማና የድርጅቱን ማህተም በእያንዳንዱ ገጽ ላይ በማሳረፍ እና ፋይናሻሉን በአንድ ፖስታ ቴክኒካሉን በአንድ ፖስታ በማሸግ ጨረታው አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ እስከ ጨረታ ማሸጊያ ሰዓት ድረስ ዩንየኑ ባለበት ቦንጋ ከተማ 01 ቀበሌ ባለ ቢሮ ለዚሁ ዓላማ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ የማይመለስ ብር 500 /አምስት መቶ ብር/ በኢት/ን/ባንክ የዩኒየኑ አካውንት ቁጥር 1000029085289 ላይ ገቢ በማድረግና ደረሰኝ በማቅረብ ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተረጋገጠ የክፊያ ማዘዣ/CPO/100,000/አንድ መቶ ሺህ ብር/ ለካፋ ሁለ ህብረት ስራ ዩኒየን በማለት አሰርተው ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ላይ ይፋ ከተደረገበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት ቅዳሜና እሁድ ጨምሮ አየር ላይ የሚቆይ ሲሆን ጨረታው በ16ኛው ቀን ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ላይ ታሽጎ በዕለቱ በ8፡30 ላይ ተጫራቾች ህጋዊ ወኪሎች/በተገኙበት ይከፈታል፣ ይሁን እንጂ ተጫራቾች ያለመገኘት ጨረታውን ከመከፈት አያስተጓጉልም።16ኛው ቀን የስራ ቀን ሆኖ ካልተገኘ በሚቀጥለው የመንግስት የስራ ቀን ይከፈታል፡፡
- ዩኒየኑ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ማሳሰቢያ፡- ማንኛውም በጨረታው ላይ መጠየቅ የፈለገ ተጫራች ተወዳዳሪ በስልክ ቁጥር፡ 09 13 10 82 40/09 19 72 39 ላይ ደውሎ መጠየቅ ይችላሉ።
በደ/ም/ኢት/ህ/ክ/መ/ በካፋ ዞን የካፋ ሁለ/ህ/ሰራ ዩኒየን
