በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በደቡብ ወሎ ዞን የጊምባ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት በ2018 በጀት አመት ለሁሉም ባለበጀት መ/ቤቶች ከዚህ በታች በሎት የተዘርዘሩትን ዕቃዎች ሎት1፡- የፅህፈት መሳሪያ፣ ሎት2፡- ጽዳት ዕቃዎች፣ ሎት3፡- ኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች፣ ሎት4፡- ፈርኒቸር፣ ሎት5፡- የመኪና ስፔር እቃዎችን በብሔራዊ ግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ለሁለተኛ ጊዜ የወጣ ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር ጊ/ከ/አሰ/ገ/ግ/ፋ/286/2018
በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በደቡብ ወሎ ዞን የጊምባ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት በ2018 በጀት አመት ለሁሉም ባለበጀት መ/ቤቶች ከዚህ በታች በሎት የተዘርዘሩትን ዕቃዎች ሎት1፡- የፅህፈት መሳሪያ፣ ሎት2፡- ጽዳት ዕቃዎች፣ ሎት3፡- ኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች፣ ሎት4፡- ፈርኒቸር፣ ሎት5፡- የመኪና ስፔር እቃዎችን በብሔራዊ ግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉ መሆኑን ይጋብዛል፡፡
- የዘመኑን የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው
- የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፣
- የግብር ክፍያ መለያ ቁጥር /TIN/ ያላቸው፣
- የግዥውመጠን ብር 200,000 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ/VAT/ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፣
- ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተ.ቁ 1-4 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው::
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 300 /ሶስት መቶ ብር ብቻ/ በመክፈል ከ/ጊ/ከ/አሰ/ገ/ግ/ፈ/ን ብ/አሰ /ቡድን ቢሮ ቁጥር 4 ማግኘት ይቻላል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢድ ቦንድ/ ለሚወዳደሩበት ዕቃውን ጠቅላላ ዋጋ 1% በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሰ.ፒ.ኦ/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆኑ ሁለት ቅጅዎች ማለትም ዋናና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በጊምባ ከተማ አሰ/ገ/ጽ/ቤት በግ/ፍ/ንብ/አሰ/ ቡድን ቢሮ ቁጥር 4 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፤ ሆኖም በጋዜጣ ከወጣበት ቀን 25/03/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ ዘወትር በስራ ሰዓት ለ15 ቀን በአየር ላይ ቆይቶ በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡30 ተዘግቶ፣ በዚህ ቀን 4፡00 ላይ ሁሉም ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የሚከፈት ይሆናል፡፡ ነገር ግን የመክፈቻው ቀን የበዓል ወይም ቅዳሜና እሁድ ከሆነ በሚቀጥለው ቀን በዚሁ በተባለው ሰዓት የሚከፈት ይሆናል፡፡
- በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ግዥና ፈይናንስ ንብረት አሰተዳደር ቡድን ቢሮ ቁጥር 4 በአካል በመገኝት ወይም በስልክ ቁጥር 033-240-58-69 በመደወል ማገኘት ይችላሉ፡፡
በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በደቡብ ወሎ ዞን የጊምባ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት
