በአዲስ አበባ ኤርፖርት ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት በተለያዩ ጊዜያት የጉምሩክ ሥነ-ሥርዓት ባለመፈጸሙ ምክንያት እና በሕገወጥ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ተይዘው የተወረሱ የተለያዩ ዕቃዎችን ባሉበት ሁኔታ በግልጽ ጨረታ እና በሐራጅ ጨረታ ለመሸጥ ይፈልጋል።
በጉምሩክ ኮሚሽን የአ/አ ኤርፖርት ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት ልዩ ልዩ ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ እና በሐራጅ ጨረታ ቁጥር
40/2018:41/2018:42/2018:43/2018:44/2018:45/2018:46/201፡47/2018 እና 48/2018
የጨረታ ማስታወቂያ
በአዲስ አበባ ኤርፖርት ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት በተለያዩ ጊዜያት የጉምሩክ ሥነ-ሥርዓት ባለመፈጸሙ ምክንያት እና በሕገወጥ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ተይዘው የተወረሱ የተለያዩ ኤሌክትሮኒክስና የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች፣ ሞባይሎች፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫዎችና ጌጣጌጥ እና አካላት፣ አልባሳት፣ ጫማዎች፣ የብርጌጣጌጥ፣ ፕላትኒየም፣ ጊርቦክስ፣ የመኪና ሞተር እና ሌሎች ባሉበት ሁኔታ በግልጽ ጨረታ እና በሐራጅ ጨረታ ቁጥር 40/2018 በቀን 02/4/2018 ዓ.ም የጨረታ ቁጥር 41/2018ዓ.ም በ06/4/2018 ዓ.ም፣ ጨረታ ቁጥር 42/2018 በ09/4/2018 ዓ.ም የጨረታ ቁጥር 43/2018 በ13/4/2018 ዓ.ም የጨረታ ቁጥር 44/2018 በ16/4/2018 ዓ.ም፣ የጨረታ ቁጥር 45/2018ዓ.ም በ20/4/2018 ዓ.ም፣ የጨረታ ቁጥር 46/2018 ዓ.ም በ23/4/2018 ዓ.ም፣ የጨረታ ቁጥር 47/2018ዓ.ም በ27/4/2018 ዓ.ም እና የጨረታ ቁጥር 48/2018ዓ.ም በ30/4/2018 ዓ.ም በመሆኑ የቀጣይ 2018 በጀት ዓመት ዕቅድ በተፈለገው መጠን ለማሳካት ለሁሉም ተደራሽነት ባለው መልኩ በጋዜጣ ማስታወቂያ እንዲወጣልን እየጠየቅን ዝርዝር መረጃ ከዚህ በታች በተራ ቁጥር 1-14 እንገልፃለን፡፡
በመሆኑም፡-
- በቅ/ጽ/ቤቱ ለሚካሄደው ጨረታ ተጫራቾች በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ሰርተፊኬት እና የዘመኑን ግብር የተከፈለ ለመሆኑ ከግብር ሰብሳቢ መሥሪያ ቤት የተሰጠ ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ማንኛውም የግልጽ ጨረታ ተጫራች ጨረታው አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ የጨረታውን ሰነድ ዘወትር በሥራ ሰዓት ከሰኞ እስከ አርብ ከ2፡00-6፡00 ሰዓት ከሰዓት በኋላ ከ7፡00-11፡00 ሰዓት እንዲሁም ቅዳሜ ጠዋት ከ2፡00-6፡00 ሰዓት የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ) በመክፈል ከአዲስ አበባ ኤርፖርት ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት ገርጂ ጉምሩክ መጋዘን ቅጥር ግቢ የውርስ ዕቃዎች አወጋገድ ቡድን በመምጣት የጨረታ ሰነድ መግዛት ይችላል፡፡
- በግልጽ ጨረታ ለመሳተፍ ተጫራቾች ለሚወዳደሩባቸው ዕቃዎች የሰጡትን ዋጋ አምስት በመቶ (5%) P (CPO) CUSTOMS COMMISSOIN ADDIS ABABA AIRPORT CUSTOM BRANCH OFFCE ስም ማሠራት ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የዕቃዎቹን ናሙና በአዲስ አበባ ኤርፖርት ጉምሩክ ካርጎ መጋዘን እና ገርጂ መጋዘን እስከ ታኅሣሥ 02/2017 ዓ.ም፣ ታኅሣሥ 6 ቀን 2018፣ ታህሣሥ 9 ቀን 2018፣ ታነሣሥ 13 ቀን 2018፣ ታኅሣሥ 16 ቀን 2018 ዓ.ም፣ ታኅሣሥ 20 ቀን 2018፣ ታኅሣሥ 23 ቀን 2018፣ ታኅሣሥ 27 ቀን 2018 ዓ.ም እና ታኅሣሥ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ በ8፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚያው ቀን በ8፡15 የሚከፈት ይሆናል።
- በጨረታው የሚወዳደሩ ተጫራቾች ለጨረታው የሚሰጡትን ዋጋ ከጨረታ ሰነዱ ጋር ተያይዘው በቀረቡት ቅጾች መሠረት ለመረጡት የዕቃዎች ኮድ የተሰጠ ዋጋ፤ የተጫራቾች ስም፣ አድራሻ፣ ፊርማና የጨረታ ማስከበሪያ ሲ.ፒ.ኦ (CPO) እና ከላይ በተ.ቁ 1 የተገለጹትን ሰነዶች ኮፒ በታሸገ ኤንቨሎፕ ላይ በመፈረም አዲስ አበባ ኤርፖርት ጉ/ቅ/ጽ/ቤት ገርጂ የውርስ ዕቃዎች አወጋገድ ቡድን ለጨረታው በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ማንኛውም ተጫራች ጨረታው ከተከፈተ በኋላ በጨረታ ሰነዱ የሰጠውን መግዣ ዋጋና መግለጫ መለወጥና ማሻሻል አይችልም፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የሰጠውን የመወዳደሪያ ዋጋ የጨረታው ግምገማ ተጠናቆ የጨረታው ውጤት እስከሚታወቅ ድረስ ፀንቶ ይቆያል፡፡
- የጨረታው አሸናፊዎች ጨረታውን ስለማሸነፋቸው ከተገለፀበት ጊዜ ጀምሮ በ05 (አምስት) ቀናት ውስጥ ያሸነፉትን ዕቃ ዋጋ ገቢ በማድረግ ዕቃውን መረከብ አለባቸው።
- ከላይ በተ/ቁ 8 በተገለጹት ቀናት ውስጥ ክፍያውን ገቢ ያላደረገ እና ንብረቱን ተረክቦ ያልወሰደ ተጫራች ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ሲፒኦ (CPO) ገቢ ሆኖ ዕቃው በድጋሚ ለሽያጭ ይቀርባል።
- በተራ ቁጥር 01 - 09 የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ በተጨማሪም በሐራጅ ጨረታ ቁጥር40/2018ዓ.ም በ02/4/2018 ዓ.ም፣ የጨረታ ቁጥር 41/2018 ዓ.ም በ06/4/2018 ዓ.ም፣ የጨረታ ቁጥር 42/2018ዓ.ም በ09/4/2018 ዓ.ም፣ የጨረታ ቁጥር 43/2018ዓ.ም በ13/4/2018 ዓ.ም፣ የጨረታ ቁጥር 44/2018ዓ.ም በ16/4/2018 ዓ.ም፣ የጨረታ ቁጥር 45/2018 ዓ.ም በ20/4/2018 ዓ.ም፣ የጨረታ ቁጥር 46/2018ዓ.ም በ23/4/2018 ዓ.ም፣ የጨረታ ቁጥር 47/2018 ዓ.ም በ27/4/2018 ዓ.ም እና የጨረታ ቁጥር 48/2018ዓ.ም በ30/4/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ በ4፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የምናካሂድ መሆኑን በዚሁ አጋጣሚ እያሳወቅን፣ የዕቃዎችን ናሙና በአዲስ አበባ ኤርፖርት ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት ገርጂ እና ካርጎ ውርስ መጋዘን በመገኘት መመልከት ይቻላል፡፡
- በሐራጅ ጨረታ የሚወዳደሩ ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ብር 100,000.00 /አንድ መቶ ሺህ/ ለየዘርፉ CUSTOMS COMMISSION ADDIS ABABA AIRPORT CUSTOM BRANCH OFFICE ስም ማስያዝ ይኖርባቸዋል፣
- ለጨረታ የቀረቡት የዕቃዎች ዋጋ ከቫት በፊት የተሰጠ መሆኑ እናሳውቃለን፡፡
- ለጨረታ የቀረቡት ዕቃዎች በተናጠል ሳይሆን ለጨረታ ሰነዱ በተሰጠ ኮድ ቁጥር ብቻ የሚሸጥ መሆኑን እናሳውቃልን፡፡
- ቅ/ጽ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ ቦሌ ኤርፖርት በስልክ ቁጥር 0116684537 እና 0116684193 ደውለው ይጠይቁ፡፡
በጉምሩክ ኮሚሽን የአ/አ ኤርፖርት ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት
