የደ/ብርሃን መምህራን ትምህርት ኮሌጅ በአጥር ግቢ ውስጥ በተለያዩ ቦታ ላይ የሚገኝ ነጭ ባህር ዛፍ /ደን/ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
የደ/ብርሃን መምህራን ትምህርት ኮሌጅ በአጥር ግቢ ውስጥ በተለያዩ ቦታ ላይ የሚገኝ ነጭ ባህር ዛፍ /ደን/ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
ሎት 1 ነጭ ባህር ዛፍ /ደን/
በዚህም መሠረት ቀጥሎ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች በግዥው ላይ እንድትሣተፉ ይጋብዛል፡፡
- በመስኩ ንግድ ፈቃድ ያለው እና የዘመኑ ግብር የከፈለ።
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያለው።
- ከላይ የተጠቀሡትን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሠነዶች ጋር ማቅረብ አለባቸው
- ስርዝ ድልዝ የማይነበብ ዋጋና በቂ ሲፒኦ ያላሲያዘ ከጨረታ ውጭ ይሆናል፡፡
- ባህር ዛፉን /ደኑን/ በሚመለከት ያለበትን ሁኔታ ግቢው ውስጥ በመገኝት ማየት ይቻላል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ለሞሉት ዋጋ 10% በባንክ በተመሠረት የክፍያ ትአዛዝ /CPO ወይንም በሁኔታ ላይ ያልተመሠረት የባንክ ዋስትና ወይም ጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው።
- የጨረታ ሠነድ የተዘጋጀው በየአይነቱ ስለሆነ እያንዳንዱን ጨረታ ሠነድ ለየብቻው ሲፒኦ በማስያዝ በተለያየ ፖስታ በማሸግ መቅረብ ይጠበቅበታል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታውን ዝርዝር ሰነድ የማይመለስ ብር 100.00 /አንድ መቶ ብር ብቻ/ በመክፈል ከቢሮ ቁጥር 013 /12 መግዛት ይችላሉ፡፡ በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ለዚህ ግዥ በተዘጋጀው የጨረታ መሆን አለበት።
- ተጫራቾች የጨረታ ሃሣባቸውን ኦርጅናልና ኮፒ በመለየት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ለዚህ ግዢ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ፡፡ CPO ኦርጅናል ፖስታ ውስጥ መሆን አለበት፡፡
- ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በአየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት ክፍት ሆኖ በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ታሸጎ በ4፡30 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ቢገኙም ባይገኙም ይከፈታል፡፡ ዕለቱ የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሣሣይ ሠዓት ታሽጎ በተመሣሣይ ሠዓት ይከፈታል፡፡
- አሸናፊው ድርጅት የአሸነፈበትን 100% ክፍያ ከፍለው ዛፍን ለማንሳት ከኮሌጁ ጋር ውል መግባት አለበት፡፡
- መስሪያ ቤቱ የጨረታ ማስከበሪያ አስይዘው ውል ካልገቡ የጨረታ ማስከበሪያ ይወርሳል፡፡
- መስሪያ ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- የደኑን አነሳስ በተመለከተ በውሉ ላይ በተገለፀው መሠረት ተፈፃሚ ይሆናል፡፡
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 011681 44 89 /0116811013/14 መጠየቅ ይችላል፡፡
የደ/ብርሃን መምህራን ትምህርት ኮሌጅ
