ድርጅታችን ሰንፔር አ.ማ. ከ2018 ዓ.ም እስከ የ2020 ዓ.ም ለተከታታይ 3(ሦስት) ዓመት የሂሳብ እንቅስቃሴውን በውጪ ኦዲተሮችን አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል።
የውጪ ኦዲተር ጨረታ ማስታወቂያ
ድርጅታችን ሰንፔር አ.ማ. ከተመሰረተ 3ኛ ዓመቱን እያስቆጠረ ይገኛል። የተመሰረተው ታህሳስ 30, 2015 ዓ.ም በተደረገ የመመስረቻ ስብሰባ ሲሆን ከዛም በኋላ ህጋዊነቱን ጠብቆ በብዙ ዘርፎች ለመሰማራት አላማውን አንግቦ የተነሳ ትልቅ ተቋም የመሆን ራዕይ ይዞ ነው። በእስካሁኑ ጉዟችን አንድ ቅድመ መደበኛ እና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከፍተን ወደ ሥራ ገብተናል። ለዚህም የሂሳብ እንቅስቃሴ ለማሰራት የውጪ ኦዲተሮችን አወዳድረን ከ2018 ዓ.ም እስከ የ2020 ዓ.ም ለተከታታይ 3(ሦስት) ዓመት የሂሳብ እንቅስቃሴውን የሚሰሩልንን በታህሳስ 26/2018 ዓ.ም ጠቅላላ ጉባኤ ላይ መሰየም እንፈልጋለን።
ስለሆነም ከቀን 08/04/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለ7 ተከታታይ የሥራ ቀናት ከጠዋቱ 2፡30 -1፡00 ድረስ በቃሊቲ KCBC 6ኛ ፎቅ ቢሮ ቁ.606 በአካል በመገኘት ጨረታውን ማስገባት የምትችሉ ሲሆን ጨረታው የሚከፈተው ቅዳሜ 18/04/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ይሆናል።
መሟላት ያለባቸው መስፈርች
- በኢትዮጵያ ሂሳብ እና ኦዲት ቦርድ የታደሰ የሙያ ፍቃድ ማቅረብ የሚችሉ
- በዘርፉ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፍቃድ ያላቸው፣
- የቫት ተመዝጋቢ የሆኑ፣
- የዘመኑን ግብር ስለመከፈላቸው
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያላቸው መሆን አለባቸው።
ለበለጠ መረጃ :- 0987972785/0986960304/0985953949
የዳሬክተሮች ቦርድ
ሰንፔር አክሲዮን ማኅበር
