የኢትዮጵያ ውሃ ሥራዎች ዲዛይንና ቁጥጥር ሥራዎች ቁጠባና ብድር የኅብረት ሥራ ማኅበር (ኢውሥዲቁሥቁብኅማ) የማኅበሩን ያለፉትን የአስር ዓመት ሂሳብ ኦዲት ለማስደረግ ተገቢውን መስፈርት የሚያሟሉ እና ሰርቲፋይድ የሆኑ የኦዲት ድርጅቶችን አወዳድሮ የአገልግሎት ስምምነት በመፈፀም ማሰራት ይፈልጋል፡፡
የኦዲት ጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር ግጨ/ኢውሥዲቁሥቁብኀማ/01/2018
የኢትዮጵያ ውሃ ሥራዎች ዲዛይንና ቁጥጥር ሥራዎች ቁጠባና ብድር የኅብረት ሥራ ማኅበር (ኢውሥዲቁሥቁብኅማ) የማኅበሩን ያለፉትን የአስር ዓመት ሂሳብ ኦዲት ለማስደረግ ተገቢውን መስፈርት የሚያሟሉ እና ሰርቲፋይድ የሆኑ የኦዲት ድርጅቶችን አወዳድሮ የአገልግሎት ስምምነት በመፈፀም ማሰራት ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም፡-
- በኢትዮጵያ የሂሳብ አያያዝና ኦዲቲንግ ቦርድ ሂሳብ ለመመርመር የሚያስችለው የሙያ ፈቃድ ያገኘ እና የሙያ ፈቃድ ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችል፣
- ወቅታዊ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያለው፣
- የታደሰ የሙያ ማረጋገጫ ፈቃድ ያለው፣
- ተመሳሳይ የኅብረት ሥራ ማኅበርን በመስራት የሙያ ልምድ ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችል፡፡
- የኅብረት ሥራ ማኅበሩን ሂሳብ ለመመርመር ብቁ ባለሙያዎችን ማቅረብ/መመደብ የሚችል፣
- ከላይ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ የኦዲት ድርጅቶች የመወዳደሪያ ሰነዶችን ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በአስር ቀናት ውስጥ በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ ዘወትር በሥራ ሰዓት ማቅረብ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን፤ የኅብረት ሥራ ማኅበሩ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም በሙሉ መሰረዝ የሚችል መሆኑን እያስታወቅን፤ ጨረታው የሚከፈተው በአስራ አንደኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ላይ ፍላጎት ያላቸው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎች በተገኙበት የሚከፈት ይሆናል።
አድራሻ፡-
የኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ኢኢ.ኮ.) ሕንጻ 1- አንደኛ ፎቅ፣ በኮርፖሬት የእቅድና ፕሮግራም ቡድን ቢሮ፣ ከመገናኛ አደባባይ ወደ ኢትዮጵያ አየር መንገድ በሚወስደው ዋና የቀለበት መንገድ ወደ የኢትዮጵያ ወጣቶችና ስፖርት ማዕከል በሚያስገባው መገንጠያ መንገድ ጫፍ ላይ ከመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የሚሰጥበት ህንጻ ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05፡፡
ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር፡- 0911421087 ደውሎ መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የውሃ ሥራዎች ዲዛይንና ቁጥጥር ድርጅት የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ የኅብረት ሥራ ማኅበር
