የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ትም/ቢሮ በ2018 በጀት ዓመት የዩኒሴፍ በጀት በመጠቀም የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች፣ ማሽኖች እና ህትመት ግዥ ለመፈጸም በሥራ መስክ የተሰማሩ የንግድ ድርጅቶች ለማወዳደር ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር 02 የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትም/ቢሮ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ትም/ቢሮ በ2018 በጀት ዓመት የዩኒሴፍ በጀት በመጠቀም
1ኛ. የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች
- Amplifier ብዛት 36
- Wireless Micraphone ብዛት 36
- Printer ብዛት 1
2ኛ. ማሽኖች
- ሲንጀር ማሽን ብዛት - 100
3ኛ. ህትመት
- ከት/ቤት ጋር የተያያዘ የፆታ ተኮር ጥቃት የሥነ-ምግባር ደንብ ብዛት - 1000 ኮፒ
- የሥርዓተ ፆታ ክበብ መመሪያ ብዛት - 1000 ኮፒ
እነኝህን ዕቃዎችን ግዥ ለመፈጸም በሥራ መስክ የተሰማሩ የንግድ ድርጅቶች ለማወዳደር ይፈልጋል።
በዚሁ መሠረት ጨረታው ላይ ለመሳተፍ የሚችሉ ተጫራቾች
- በዘርፉ ህጋዊ የታደሰ የንግድ ሥራ ፍቃዳቸውን የንግድ ምዝገባ ሰርተፍኬታቸውን በግብር ከፋይነት ተመዝግቦ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያለውና ተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡበትን የምዝገባ ወረቀት፣ የዘመኑን የግብር ግዴታውን የተወጣ እና በአቅራቢዎች ዝርዝር የተመዘገበበት፣ መረጃ ፎቶ ኮፒ አያይዞ ማቅረብ ይጠበቅበታል።
- ተጫራቾች በትምህርት ቢሮ ቁጥር 18 በመቅረብ ለሥራው የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ለእያንዳንዱ ብር 300 /ሦስት መቶ ብር/ በመክፈል ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት ዘወትር በሥራ ሰዓት መግዛት ይችላሉ።
- የፋይናንሻል ሰነዳቸውን አንድ ኦርጅናል እና እንድ ኮፒ ሰነድ ለየብቻ አሽጎ በማቅረብ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በቢሮ ቁጥር 18 ለዚህ ለተባለው በተዘጋጀ ሣጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና CPO ወይም የባንክ ጋራንቲ የሚገልጽ
1ኛ. ለኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች የገንዘብ መጠን ብር 30,000 /ሰላሳ ሺህ ብር ለጨረታ ማስከበሪያ
2ኛ. ለልብስ ስፌት ማሽን የገንዘብ መጠን ብር 30,000 /ሰላሳ ሺህ ብር ለጨረታ ማስከበሪያ
3ኛ. ለህትመት የገንዘብ መጠን ብር 30,000 /ሰላሳ ሺህ ብር ለጨረታ ማስከበሪያ ማቅረብ አለባቸው።
- ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት ቆይቶ በ16ኛው የሥራ ቀን ከቀኑ 6፡30 ሰዓት ታሽጎ 8፡30 ሰዓት ይከፈታል። 16ኛው ቀን የሥራ ቀን ካልሆነ በቀጣይ የሥራ ቀን ላይ በተባለው ቦታና ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል ።
- መ/ቤቱ በጨረታው ላይ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር 0467752359 / 0916863055 መጠየቅ ይችላሉ።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ትም/ቢሮ
