በአቃ/ቃ/ክ/ከተማ ሳሪስ ጤና ጣቢያ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ያገለገሉ እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ እና በግቢው ውስጥ ያሉ ዛፎችን ማስቆረጥ ይፈልጋል።
ያገለገሉ እቃዎች ሽያጭ እና ዛፍ
መቁረጥ ሥራ ጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 01/2018
በአቃ/ቃ/ክ/ከተማ ሳሪስ ጤና ጣቢያ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ያገለገሉ እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ እና በግቢው ውስጥ ያሉ ዛፎችን ማስቆረጥ ይፈልጋል።
- ሎት 1 የተለያዩ ከ24 አይነት በላይ ያገለገሉ እቃዎች ሽያጭ
- ሎት 2 25 ትላልቅ ዛፎች ማስቆረጥ ስራ
ከላይ የተዘረዘሩት ሎቶች ላይ መጫረት የምትፈልጉ ተጫራቾች
- በዘርፉ ሕጋዊ ፍቃድ ያላቸው፣ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፤ የዘመኑን ግብር የከፈሉ መሆናቸውን የሚገልፅ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፣ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት፣ የግብር ከፋይነት የምስክር ወረቀት ያላቸው እና ቫት (VAT) ተመዝጋቢመሆናቸውን የሚገልፅ የምስክር ወረቀት እነዚህን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች ጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 10 የስራ ቀናት የጨረታ ሰነዱን ከሳሪስ ጤና ጣቢያ ከፋ ቡድን ቢሮ ቁጥር 35 የማይመለስ ብር 200.00 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ዋጋ ማለትም ሎት1 ያገለገሉ የቢሮ እቃዎች ሽያጭ 7,000.00 (ሰባት ሺህ ብር) እና ሎት 2 (የዛፍ መቁረጥ ሥራ) 7,000.00 (ሰባት ሺህ ብር ብቻ) በባንክ በተረጋገጠ ቼክ ወይም ሲፒኦ (CPO) በአድራሻችን ከጨረታ ሰነድ ጋር በፖስታ በማሸግ ማቅረብ አለባቸው።
- ጨረታው ጋዜጣ ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 10ኛው የሥራ ቀን አየር ላይ ውሎ በ11ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ላይ ታሽጎ በዛኑ ቀን ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው ባሉበት ሳሪስ ጤና ጣቢያ ቢሮ ቁጥር 31 ይከፈታል። ነገር ግን ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው ባይገኙም የጨረታ ሂደት በተቀመጠው መሠረት ይካሄዳል። የጨረታ መዝጊያ እና መክፈቻ ቀን ዝግ ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ይሆናል።
- ተጫራቾች ከመሥሪያ ቤቱ በገዙት የጨረታ ሰነድ ላይ ብቻ የዋጋ ዝርዝር ሞልተው ማቅረብ አለበቸው።
- ተጫራቾች ሁሉንም በዝርዝር የቀረቡትን ያገለገሉ እቃዎች ሙሉ ለሙሉ ዋጋ መሙላት ይጠበቅበታል።
- ሎት 1 (የተለያዩ ከ24 ዓይነት በላይ ያገለገሉ እቃዎች ሽያጭ) ላይ ለሚወዳደሩ ተጫራቾች አሸናፊው ተወዳድሮ ማሸነፉን በደብዳቤ ከተገለፀለት ቀን ጀምሮ በ3 ቀናት ውስጥ ያሸነፈበትን ገንዘብ ገቢ በማድረግ እቃውን ከቦታው ማንሳት ያለበት ሲሆን ይህ የማይሆን ከሆነ ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዘው ዋስትና የሚወረስ ይሆናል።
- በሎት 2 (25 ትላልቅ ዛፎች ማስቆረጥ ሥራ) ዛፎቹን በጥንቃቄ በንብረትም ሆነ በሰው ላይ ምንም ዓይነት አደጋ በማያደርስ ሁኔታ በመቁረጥ ሙሉ በሙሉ በራሳቸው ወጪ ከግቢው እንስተው መውሰድ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች ዋጋ ሲሞሉ ስርዝ ድልዝ መኖር የለበትም፤
- ተጫራቾ ዋጋ ሲሞሉ ቫትን አካቶ መሆን አለበት።
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- አቃ/ቃ/ክ/ከ/ወረዳ 06 ሳሪስ ጤና ጣቢያ 3F ፊት ለፊት ከሙኒከ ሆቴል አጠገብ
ስልክ ቁጥር፡- 0114-70-98-59/0114-70-79-77
የሳሪስ ጤና ጣቢያ
