አባ ወልደ ትንሣኤ ግዛው የእናቶችና ሕፃናት በጎ አድራጎት ሀገር በቀል ድርጅት እ.ኤ.ዘ.አ ከ2025 ጀምሮ ለድርጅቱና በሥሩ ለሚገኘው ለቦሌ ቡልቡላ አቡነ ዲዮስቆሮስ መካከለኛ ክሊኒክ ዓመታዊ ሂሣባቸውን በሕጋዊ የውጭ ኦዲተሮች አወዳድሮ ማስመርመር ይፈልጋል።
የኦዲት ሥራ ጨረታ ማስታወቂያ
አባ ወልደ ትንሣኤ ግዛው የእናቶችና ሕፃናት በጎ አድራጎት ሀገር በቀል ድርጅት እ.ኤ.ዘ.አ ከ2025 ጀምሮ ለድርጅቱና በሥሩ ለሚገኘው ለቦሌ ቡልቡላ አቡነ ዲዮስቆሮስ መካከለኛ ክሊኒክ ዓመታዊ ሂሣባቸውን በሕጋዊ የውጭ ኦዲተሮች አወዳድሮ ማስመርመር ይፈልጋል።
ስለሆነም ለመወዳደር የምትፈልጉ ሁሉ የሚከተሉትን መስፈርቶች በማሟላት ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ዕለት አንስቶ በ15 /አሥራ አምስት/ ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ ከታች በተቀመጠው አድራሻ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ የመወዳደሪያ ሰነድ ማቅረብ የምትችሉ መሆኑን እናስታውቃለን።
- የታደሰ የሙያ ማረጋገጫ ሠርተፍኬት፣
- የታደሰ ንግድ ፈቃድ፣
- የዘመኑ ግብር ስለመክፈሉ መረጃ፣
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር፣
- ከፌዴራል ወይም ከክልል ኦዲተር መ/ቤት ለበጀት ዓመቱ የታደሰ ፈቃድ፣
- የ2024 ዓ.ም. ሂሳብን መነሻ በማድረግ የ2025 ሂሣብን በማቅረብ የሦስት ዓመት ውል ለመዋዋል ፈቃደኛ የሆነ ሁሉ።
አድራሻ፡- ቦሌ ክ/ከተማ፣ ወረዳ 12 /ቦሌ ቡልቡላ/ 40/60 ኮንዶሚኒየም ብሎክ 25 ፊት ለፊት ወይም አዋሽ ባንክ ቡልቡላ 40/60 ቅርንጫፍ ፊት ለፊት።
የሂሣቡን መጠንና ሌሎች ተጨማሪ መረጃ ለምትፈልጉ ከዚህ በታች በተጠቀሱት የስልክ አድራሻ በመደወል ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
ስልክ ቁጥር 0114 71 40 79 ወይም 0911 22 57 43
አባ ወልደ ትንሣኤ ግዛው የእናቶችና ሕፃናት በጎ አድራጎት ድርጅት
