ኩባንያችን ትራኮን ትሬዲንግ ኃ.የተ.የግል ማህበር የተለያዩ ያገለገሉ መኪኖች እና ፎረክሊፈት/JCB/ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል::
ትራኮን ትሬዲንግ ኃ.የተ.የግል ማህበር
የጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር ትት/ግዥ079/2018
ኩባንያችን ትራኮን ትሬዲንግ ኃ.የተ.የግል ማህበር የተለያዩ ያገለገሉ መኪኖች እና ፎረክሊፍት/JCB/ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል::
ስለሆነም ከዚህ በታች የተዘረዘሩት መስፈርቶች በማሟላት እንድትወዳደሩ ይጋብዛል።
- ተጫራቾች በዘርፉ ወይም በተመሳሳይ ዘርፍ የተሰማሩ 2018 ዓ.ም ህጋዊና የታደሰ የንግድ ሥራ ፈቃድ ያለው፤ የተ.እ.ታ ተመዝጋቢ የሆነ እና የቲን ሰርተፍኬት ያለው ማንኛዉም አገልግሎት አቅራቢ የዋጋ ማቅረቢያ ማቅረብ ይችላል።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ /ቢድ ቦንድ/ የጠቅላላዉን 2% ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- የጨረታዉን ሰነድ ጅሞ 3 አጫሉ መንገድ አካባቢ በሚገኘዉ ትራኮን ዋና መ/ቤት ጨረታዉ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ጥር 9, 2018 ዓ.ም ድረስ የማይመለስ ብር 200 በመክፈል ሰነድ መግዛት ይቻላሉ።
- ተጫራቾች የጫረታ ሰነዶቻቸዉን በታሸገ ፖስታ ጥር 9, 2018 ዓ.ም ከቀኑ 4፡00 ስአት ድረስ ብቻ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው ጥር 9, 2018 ዓ.ም ከቀኑ 4፡00 ሰአት ተዘግቶ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎች በተገኙበት ጅሞ 3 አጫሉ መንገድ አካባቢ በሚገኘዉ ትራኮን ዋና መ/ቤት 4፡30 ይከፈታል።
- ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 0118722174/0911455448/
0929918416/0929040439 ግዥ ክፍል መጠየቅ ይቻላል።
ትራኮን ትሬዲንግ ኃ.የተ.የግል ማህበር
