በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 የሚገኘው ፍልውሃና ፊት በር በአልታድ መንደር ሸማቾች ኃ/የተ/የህ/ስራ ማህበር የ2017 ዓ.ም በጀት አመት የስራ እንቅስቃሴ ሂሳብ ባለሙያ አወዳድሮ ለማስመርመር ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 የሚገኘው ፍልውሃና ፊት በር በአልታድ መንደር ሸማቾች ኃ/የተ/የህ/ስራ ማህበር የ2017 ዓ.ም በጀት አመት የስራ እንቅስቃሴ ሂሳብ ባለሙያ አወዳድሮ ለማስመርመር ይፈልጋል።
በዚሁ መሰረት መወዳደር የምትፈልጉ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ህብረት ስራ ኤጀንሲ (ኮሚሽን) የህብረት ስራ ማህበራትን ሂሳብ በውክልና ለማስመርምር ባወጣው ደንብ ቁጥር 171/2016 ምዕራፍ 4 ከቁጥር 44/2016 ዓ.ም መሰረት፡
- የኢትዮጲያ ሂሳብ አያያዝና ኦዲት ቦርድ ወይም እሱ ከሚወክለው አካል ሂሳብ ለመመርመር የሚያሥችለውን የሙያ ፈቃድ ያገኘ እና የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችል (የምትችል)
- በአገሪቱ ህግ መሰረት የኦዲት ስራ ለመስራት የሚያሥችል ወቅታዊ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያለው/ያለት
- የህብረት ስራ ማህበራት ሂሳብ ምርመራ በተመለከተ ከፌደራል ህብረት ስራ ኮሚሽን እንዲሁም ከአዲስ አበባ ህብረት ስራ ኮሚሽን ወይም ከሌሎች ህጋዊ አካላት ስልጠና የወሰደ እና ማስረጃ ማቅረብ የሚችል።
- ተወካይ ሂሳብ መርማሪ ወይም ከሂሳብ መርማሪው ቡድን አባለት ውስጥ ቢያንስ አንዱ ከዚህ በፊት የህብረት ስራ ማህበራትን ሂሳብ የመረመረ ቢሆን ቅድሚያ ይሰጠዋል።
- የህብረት ስራ ማህበራት ሂሳብ ለመመርምር ብቁ ባለሙያዎችን በስራ ላይ ማሰማራት የሚችል ይህ ሳይሆን ቀርቶ ለሚከተለው ማንኛውንም ኪሳራ እና ችግር አስቀድሞ ሃላፊነቱን የሚወስድ
- እንደ አስፈላጊነቱ አግባብ ባለው ባለስልጣን የሚጠየቁ ሌሎች መረጃዎችን ማቅረብ የሚችል መሆን አለበት
- ኮሚሽኑ አዳዲስ አሰራሮች ላይ የሚሰጣቸውን ስልጠናዎች ለመውሰድ ፍቃደኛ የሆነ
- ህጋዊ የገንዘብ መቀበያ ደረሰኝ: TinNo: VAT እና ማህተም ያለው/ት
- 2% ሲፒኦ ማስያዝ የሚችል/ትችል
ተወዳዳሪዎች ከፍል ውሃ እና ፊት በር በአልታድ መንደር ሸማቾች ኃ/የተ/የህ/ስራ ማህበር ቢሮ ቁጥር 001 የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ በብር 500.00 /አምስት መቶ ብር/ በመግዛት ከዚህ በላይ የተዘረዘሩትን ማስረጃዎች በማያያዝ በፓስታ በማሸግ ከቀን 25/04/2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 4/5/2018 ዓ.ም በስራ ሰዓት ከጠዋቱ 2፡30-11፡00 ሰዓት ሰነዱን የገዛችሁበት ቢሮ ቁጥር 001 በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ እንድታስገቡ እና ጨረታውም 5/5/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ህጋዊ ተጫራቾች ወይም በወኪሎቻቸው እና ታዛቢዎች በተገኙበት በይፋ ይከፈታል።
ማሳሰቢያ፡ ጨረታው በሚከፈትበት ጊዜ በሰዓቱ ሳይገኙ ቢቀርም በተገኘው አባላት ይከፈታል ባለመገኘት ለሚቀርብ ቅሬታ ተቀባይነት የለውም።
