ብርሃን ባንክ አ.ማ አዲስ አበባ ከተማ የካ ክ/ከተማ ወረዳ 11 ወሰን አካባቢ ሂል ሳይድ ት/ቤት ፊት ለፊት የሚገኝ የጊቢው ጠቅላላ ስፋት 294 ካ/ሜ. የሆነ፣ ቤዝመንት፣ ምድር ቤት፣ ሶስት ወለል እና ከኋላ ሰርቪስ ክፍሎች ያሉት መኖሪያ ቤት (B+G+3) ማከራየት ይፈልጋል።
የመኖሪያ ቤት ኪራይ ጨረታ ማስታወቂያ
ብርሃን ባንክ አ.ማ አዲስ አበባ ከተማ የካ ክ/ከተማ ወረዳ 11 ወሰን አካባቢ ሂል ሳይድ ት/ቤት ፊት ለፊት የሚገኝ የጊቢው ጠቅላላ ስፋት 294 ካ/ሜ. የሆነ፣ ቤዝመንት፣ ምድር ቤት፣ ሶስት ወለል እና ከኋላ ሰርቪስ ክፍሎች ያሉት መኖሪያ ቤት (B+G+3) ማከራየት ይፈልጋል።
ቤቱ የሚከራየዉ፤ ለመኖሪያ ቤት፣ ለቢሮ አገለግሎት፣ ለክሊኒክ እና ለሌሎች ሕጋዊ ስራዎች ሲሆን ተከራዮች ቤቱን ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ አስከ መዝጊያው ባሉት ቀናት ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት አስከ ቀኑ 11፡00 ሰዓት መጎብኘት ይችላሉ።
ቤቱን ለመከራየት ፍላጎት ያላቸዉ ተጫራቾች ታክስን ጨምሮ የሚከፍሉትን ወርሃዊ የኪራይ ዋጋ እና የቅድመ ክፍያ መጠን የምን ያህል ወራት/አመት እንደሚከፍሉ በማካተት በታሸገ ኢንቨሎፕ እስከ ጥር 13 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ድረስ የባንኩ ዋና መስሪያ ቤት በሚገኝበት ቦሌ የቀድሞዉ ብራስ ሆስፒታል ከነበረበት ቦታ ፊት ለፊት በሚገኘዉ ወመሳድኮ ህንፃ 2ኛ ፎቅ ፕሮፐርቲ እና ሎጂስቲክስ አስተዳደር መምሪያ ቢሮ ለቤቱ ኪራይ ጨረታ በተዘጋጀ ሳጥን ማስገባት ይችላሉ።
ጨረታው ጥር 13 ቀን 2018 ዓ/ም ከቀነ 8፡30 ሰዓት ላይ ቤቱን ለመከራየት የፈለጉ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት የባንኩ ዋና መስሪያ ቤት በሚገኝበት ቦሌ ብራስ ሆስፒታል ከነበረበት ቦታ ፊት ለፊት በሚገኘዉ ወመሳድኮ ህንፃ 25 ፎቅ ፕሮፐርቲ እና ሎጂስቲክስ አስተዳደር መምሪያ ቢሮ ይከፈታል። ባንኩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ ለሙሉ የመሰረዝ መብት አለው፡፡
ተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0998454424 / 0116631729 ማግኘት ይችላሉ።
ብርሃን ባንክ አ.ማ.
