በአማራ ደን ኢንተርፕራይዝ ዋና ጽ/ቤት በተለያዩ አካባቢዎች የተገኘውን ቁም ደን ባለበት ሁኔታ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
የቁም ደን ሽያጭ ጨረታ ማስታወቂያ
በአማራ ደን ኢንተርፕራይዝ ዋና ጽ/ቤት ደ/ጎንደር ዞን ጉና በጌምድር ወረዳ አርጋ ድድም ቀበሌ እንጨትና ዋልጋሜዳ የመንግስት ደን ውስጥ 15,715,80 ሜ/ኩብ ነጭ ባህርዛፍ 4,047.73 ሜ/ኩብ የፌ/ፅድ በድምሩ 19,763.53 ሜ/ኩብ ቁም ደን፣ አዊ ዞን ባንጃ ወረዳ በአረፅ ቀበሌ በተርያ የመንግስት ደን ውስጥ የሚገኘውን 1,044.92 ሜ/ኩብ የፈ/ጽድ ቁም እና በሰ/ሸዋ ዞን ባሶና ወረና ወረዳ ጉዶ በረት ቀበሌ ዱቤ አገር የመንግስት ደን ውስጥ የሚገኘውን ሁለት ክፍልፋይ 7,167.50 ሜ/ኩብ፣ ቀርሳ የመንግስት ደን ውስጥ በዘጠኝ ክፍልፋይ የተከፈለ ብዛቱ 1,828.38 ሜ/ኩብ እና ድንኳን የመንግስት ደን ውስጥ ብዛቱ 427 98 ሜ/ኩብ በድምሩ 9,423.86 ሜ/ኩብ የነጭ ባህርዛፍ ቁም ደን ቁም እና በምዕ/ጎጃም ዞን ፍኖተ ሰላም ወረዳ ቀረር የመንግስት ደን ውስጥ 14 ክፍልፋይ የምርት መጠኑ 3,791.159 ሜ/ኩብ ቀይ ባህርዛፍ ቁም ደን ባለበት ሁኔታ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም ተጫራቾች:
1. ተጫራቾች በዘርፉ የታደሰ የንግድ ሥራ ፈቃድና የግብር ከፋይ ምዝገባ ሰርቲፍኬት ያላቸዉና የዘመኑን ግብር የከፈሉ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
2. የሽያጩ መጠን 200,000.00 /ሁለት መቶ ሺህ ብር በላይ ከሆነ የተእታ /VAT/ ምዝገባ የምስክር ወረቀት ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
3. ለጨረታ የቀረቡትን ቁም ደን ማየት የሚፈልጉ ተጫራቾች ዘወትር በሥራ ስዓት በቦታው ተገኝተው ማየት ይችላሉ፡፡
4. የጨረታ ሰነዱን ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 10 የስራ ቀናት ውስጥ /ቅዳሜ ግማሽ ቀን ጨምሮ/ በአማራ ደን ኢንተርፕራይዝ ዋና ጽ/ቤት ባሕርዳር ቀበሌ 14 አዲሱ መናኸሪያ ጀርባ እንስሳት ማዳቀያ ግቢ ዉስጥ ከኢንተርፕራይዙ ቢሮ ቁጥር 06 እና በሁሉም ቅ/ጽ/ቤቶች የማይመለስ 200.00 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል መግዛት ይችላሉ፡፡
5. ተጫራቾች ለመግዛት የሚፈልጉትን ምርት ጠቅላላ ዋጋ 2% የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (Bid Bond) በባንክ የተረጋገጠ የክፍያ ማዘዣ/CPO/ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
6. ተጫራቾች መግዛት የሚፈልጉትን ቁም ደን በኦሪጅናል ዋጋ መሙያ ቅጽ የሚገዙበትን ነጠላና ጠቅላላ ዋጋ ስምና አድራሻቸዉን በመፃፍ ፈርመው በመሙያው ሰነዱ ላይ ማህተም በማስቀመጥ የታሸገውን የጨረታ ፖስታ በአማራ ደን ኢንተርፕራይዝ ዋና ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 06፣ ደ/ብርሃንና ኮምቦልቻ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ቁም ደን የጨረታ ሽያጭ ማስታወቂያ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዉስጥ ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ (ቅዳሜ ግማሽ ቀን ጨምሮ) እስከ መጨረሻው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል። ጨረታው በዚሁ ቀን በ4፡00 ሰዓት ላይ ሳጥኑ ታሽጎ በ4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ ይሁን እንጅ ተጫራቾች ባይገኙም ይከፈታል፡፡
7. ተጫራቾች የሚሞሉት ነጠላና ጠቅላላ ዋጋ 15% ተእታን አይጨምርም፡፡ ሆኖም አሸናፊው ባሸነፈበት ዋጋ ላይ 15% ተእታን ጨምሮ ይከፍላል።
8. ተጫራቾች ቅልቅል ደን ተብሎ የቀረበውን ሁሉንም ክፍልፋይ መሙላት ይጠበቅባቸዋል፡፡
9. በሌላ ተጫራች ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ አይቻልም፡፡
10. ኢንተርፕራይዙ ጨረታውን በሙሉ ሆነ በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
11. ለተጨማሪ መረጃ በስልከ ቁጥር ባ/ዳር 0582263095፣ ደ/ታቦር 0584410306፣ ደ/ብርሃን 0116375017፤ እንጅባራ 0582270485፣ ደ/ማርቆስ 0588719004፣ ኮ/ቻ 0914716636 ደውሎ መጠየቅ ይችላል፡፡
የአማራ ደን ኢንተርፕራይዝ ዋና ጽ/ቤት
ባሕር ዳር
