የኦሮሚያ የግብርና ህብረት ሥራ ማህበራት ፌዴሬሽን ኃ/የተወ. እና ከአይ. ዲ. ኤች, ፕሮጀክት ጋር በቅንጅት ጋር በመተባበር የተሰሩ ስራዎችን ሂሳብ ከመስከረም 1 ቀን 2024 ጀምሮ እ.ኤ.አ እስከ ታህሳስ 31 ቀን 2025 እ.ኤ.አ የፕሮጀክቱን ሂሳብ ለማስመርመር በጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡
የፕሮጀክት ሂሳብ ምርመራ አገልግሎት ግዥ ማስታወቂያ
የኦሮሚያ የግብርና ህብረት ሥራ ማህበራት ፌዴሬሽን ኃ/የተወ. እና ከአይ. ዲ. ኤች, ፕሮጀክት ጋር በቅንጅት ጋር በመተባበር የተሰሩ ስራዎችን ሂሳብ ከመስከረም 1 ቀን 2024 ጀምሮ እ.ኤ.አ እስከ ታህሳስ 31 ቀን 2025 እ.ኤ.አ የፕሮጀክቱን ሂሳብ ለማስመርመር በጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም በመስኩ የተሰማሩ ተጫራቾች
1. በፌዴራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት የተመዘገቡና የኦዲት ሥራ ፈቃድ ያላቸው ስለመሆኑ የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
2. የአዲት ድርጀቱ አጠቃላይ የሥራ ልምድ ማቅረብ አለባቸው፡፡
3. የአዲት ድርጅቱን የሰው ኃይል ብቃት ለማየት የሚያስችል ቋሚ የኦዲት ባለሙያዎችን በተመለከተ ጠቅለል ያለ መረጃ /ማስረጃ መቅረብ አለበት፡፡
4. በአዲት ሥራ ላይ የሚመደቡ የኦዲተሮች ብዛት፣ የትምህርት ደረጃ፣ የሥራ ደረጃና የሥራ ልምድ /ዝርዝር/ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
5. አሸናፊ ሆኖ ቢመረጥ ሥራውን ለመጀመር የሚወሰድበት ጊዜና ሥራውን ከጀመረ በኋላ ሪፖርቱን የሚያቀርብበት ጊዜ/ በሥራ ቀናት መግለጽ አለበት፡፡
6. ከዚህ በፊት ከመረመሯቸው ተመሳሳይ ከሆኑ ድርጅቶች ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችል መሆን አለበት።
7. የበጀት ዓመቱን ሂሳብ ለመመርመር የሚያስፈልገው የአገልግሎት ክፍያ/ዋጋ/ማቅረብ አለበት፡፡
8. የኦዲት ድርጅቱ ኦሮሚኛ ማንባብ እና መጻፍ የሚችል መሆን አለባቸው፡፡
9. የኦዲት ድርጅቱ የሂሳቡን ሪፖርት በእንግሊዝኛ አዘጋጅቶ ለፕሮጀክቱ ዶነር ማቅረብ የሚችል፤
10. የኦዲት ድርጅቱ የፕሮጀክቱ ዶነሮች የሚጠይቃቸውን ጥያቄዎች በቂ መልስ መስጠት የሚችል
11. በጨረታው የሚወዳደሩት ሕጋዊ የታደሰ የንግድ ፍቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉ ስለመሆናቸው የማስረጃውን ኮፒ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
12. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን ቴክኒካሉን ኮፒና ኦርጅናል እና ፋይናንሻሉን ኮፒና ኦርጅናል ለየብቻ ማቅረብ አለባቸው።
13. ተጫራቾች የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል ጨረታ ሰነዱን ከኦሮሚያ ግብርና ህብረት ሥራ ማህበራት ፌዴሬሽን ይህ ጨረታ በማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 10 ተከታታይ ቀናት ብቻ መውሰድ ይቻላል።
14. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ማስከበሪያ የ90 ቀን ዋስትና ያለው ቢድ ቦንድ፣ ሲፒኦ ከጨረታ መክፈቻ ቀን ጀምሮ የሚቆጠር የዋጋውን 5% (አምስት ፐርሰንት) በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ከዶክመንት ጋር ተያይዞ መቅረብ አለበት፡፡
15. ጨረታው በ11ኛው ቀን 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዕለቱ በ4፡30 ሰዓት በመገኘት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት አዲስ አበባ ጀሞ ሚካኤል ጎን ኦሮሚያ የግብርና ህብረት ሥራ ማህበራት ፈዴሬሽን ኃ/ የተወ. ዋና መስሪያ ቤት ይከፈታል፡፡
16. የተጠቀሱትን መስፈርቶች ያላሟላ ተጫራች ውድቅ ይደረጋል፡፡
አድራሻ፡- አዲስ አበባ ጀሞ ሚካኤል አደባባይ ሚካኤል ቤ/ክ ጎን OACF ህንፃ 6ኛ ፎቅ ዋና ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 12 ስልክ፡- 0910645442
የኦሮሚያ የግብርና ህብረት ሥራ ማህበራት ፌዴሬሽን ኃ/የተወ.
