በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስ የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት ስር ላለው ባህልና ኪነ- ጥበብ ጽ/ቤት በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የሚያስፈልጋቸውን የሙዚቃ መሳሪያ፣ የባህል ቡድን አልባሳት፣ የልጆች መጫወቻ እና የካፍቴሪያ መግዛት ይፈልጋል።
ሶስተኛ ዙር ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስ የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት ስር ላለው ባህልና ኪነ- ጥበብ ጽ/ቤት በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የሚያስፈልጋቸውን የሙዚቃ መሳሪያ፣ የባህል ቡድን አልባሳት፣ የልጆች መጫወቻ እና የካፍቴሪያ መግዛት ይፈልጋል።
በዚሁ መሰረት ለእያንዳንዱ ሎቶች ሲፒኦ
ሎት 1 የባህል ልብስ አልባሳት - CPO 10,000.00
ሎት 2 የባህል ቡድን ሙዚቃ መሳሪያ - CPO 10,000.00
ሎት 3 የልጆች መጫወቻ እና ካፍቴሪያ - CPO 10,000.00
ብቃት ያላቸውንና በመስኩ የተሰማሩ ተጫራቾችን አወዳድሮ ግዥ መፈጸም ይፈልጋል።
በዚሁ መሰረት፡-
1. በጨረታው ለመወዳደር ፍላጎት ያላቸው ተጫራቾች የታደሰ የንግድ ፍቃድ ያላቸው የዘመኑን ግብር የከፈሉ የቲን እና የቫት ተመዝጋቢ የሆኑ እና የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ።
2. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒአ ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ የሚችሉ።
3. ተጫራቾች ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት እለት አንስቶ በተከታታይ 10 የስራ ቀናት የማይመለስ ብር 250 /ሁለት መቶ ሃምሳ ብር በመክፈል በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ፐብሊከ ሰርቪስ የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት የመንግስት ግዥ ክፍል 6ኛ ፎቅ በመምጣት የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።
4. ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዳቸውን በታሸገ ኤንቨሎፕ ማስታወቂያው ከወጣበት እለት ጀምሮ ለተከታታይ 10 የስራ ቀናት በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስ የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት የመንግስት ግዥ ከፍል 6ኛ ፎቅ ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
5. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአስረኛው ቀን በ11፡30 ታሽጎ በአስራ አንደኛው ቀን በ4፡30 ሰዓት በክፍለ ከተማው 6ኛ ፎቅ ይከፈታል። የመከፈቻ ቀኑ ቅዳሜና እሁድ ወይም የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል።
6. ተጫራቾች የጨረታ ሳጥን ከመከፈቱ በፊት ለተወዳደሩባቸው ሎት 1 ሎት 2 ሎት 3 በቀረበው የፍላጎት መግለጫ መሰረት የተሟላ የፍላጎት መግለጫ ማዘጋጀትና ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
7. ተጫራቾች የሚወዳደሩባቸውን እቃዎች ለእያንዳንዱ ከቫት ጋር ያለውን ዋጋ ማስቀመጥ ይጠበቅባቸዋል።
8. የዘገየ ጨረታና በጨረታ መክፈቻ ላይ ያልተነበበ ጨረታ ተቀባይነት የለውም።
9. ለአሸናፊ ተጫራቾች ያሸነፈባቸውን እቃዎች በራሳቸው ትራንስፖርት ግዥ ፈፃሚው መስሪያቤት ድረስ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
10. መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
በተጨማሪ ሰማብራሪያ ጥያቄ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስ የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት የመንግስት ግዥ ከፍል 6ኛ ፎቅ ስልክ ቁጥር 09-12-88-50-86
በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስ የሰው ሀብት ልማት ፑል አስተባባሪ ጽ/ቤት
