የአዋሽ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት የጉምሩክ ህግን ተላልፈው የተያዙ የተለያዩ የኮንትሮባንድ እቃዎችን በ 20/05/2018 ዓ/ም በግልጽና በሀራጅ ጨረታ በኦክሽን ኢትዮጵያ (auction Ethiopia) መተግበሪያ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የአዋሽ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት የጉምሩክ ህግን ተላልፈው የተያዙ የተለያዩ የኮንትሮባንድ እቃዎችን በ 20/05/2018 ዓ/ም በግልጽና በሀራጅ ጨረታ በኦክሽን ኢትዮጵያ (auction Ethiopia) መተግበሪያ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል። በመሆኑም በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች መተግበሪያውን ከአፕ ስቶር ወይም ፕሌይ ስቶር auction Ethiopia ብለው በማውረድ ወይም www.auction.et ላይ በመመዝገብና የጨረታ ሰነዱን በማየት የሚከተሉትን ዝርዝር መስፈርቶች በማሟላት በጨረታው መሳተፍ የምትችሉ ሲሆን የእቃዎችን ሳምፕልም ከኦክሽን ኢትዮጵያ ድህረ-ገፅ (Auction Ethiopia page) ወይም አዋሽ ጉምሩክ ቅ/ፅ/ቤት በአካል በመገኘት ወይም በቴሌግራም እንዲላክልዎት በማድረግ ማየት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
የጨረታ መስፈርቶች፡
1. ለጨረታ በቀረቡት ዕቃዎች ላይ ለመሳተፍ የሚያስፈልግ ተጫራች በጨረታ በሚሸጡ ዕቃዎች ጋር በዘርፉ የታደሰ ንግድ ፍቃድ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርተፍኬት፣ የዘመኑን ግብር የከፈለ ስለመሆኑ ክሊራንሰ (Clearance) እና የተጨማሪ እሴት ታክስ እንቅሰቃሴያቸውን ለታክስ ማዕከሉ ያሳወቁበት፣ በቅርብ ጊዜ የተሰጣቸው የምስክር ወረቀት እና የመለያ ቁጥሩን ከመጫረቻ ሰነዱ ጋር አያይዞ በሲስተም አታች ማድረግ ይኖርባቸዋል።
|
ተ.ቁ |
የጨረታ ቦታ |
የጨረታ ዓይነት |
ለጨረታ የቀረቡ እቃዎች |
የዕቃዎች መመልከቻ ቀን በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ |
የጨረታው የመዝጊያ እና የመክፈቻ ቀንና ሰዓት |
|
1 |
አዋሽ ጉ/ቅ/ፅ/ቤት |
ግልፅና ሐራጅ |
ጫማዎች፣ አልባሳት፣ ኮስሞቲክስ፣ የመኪና መለዋወጫ፣ የኤሌክትሪክ እቃ፣ የሞባይል ቀፎና አክሰሰሪ፣ ኮፐር ዋየር እና ልዩ ልዩ እቃዎች
|
ለግልፅ ጨረታ በ 20/05/2018 እሮብ ጠዋቱ 3፡45 እና ለሃራጅ ጨረታ እስከ 4:45 |
ለግልፅ ጨረታ እስከ 20/05/18 ጠዋቱ 4፡00 ሲሆን ለሃራጅ ጨረታ የመጀመሪያ 5፡00 ይሆናል። |
2. ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ዘወትር በስራ ሰዓት እስከ 20/05/2018 ዓ/ም ከኦክሽን ኢትዮጵያ ድህረ-ገፅ (Auction Ethiopia page) ማየት ይችላሉ፡፡
3. ለግልፅ ጨረታ ለመሳተፍ ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (cpo) የሚወዳደሩበት እቃ ኮድ 5% እንዲሁም ለሃራጅ ጨረታ ለሚወዳደሩበት እቃ ኮድ ብር 100,000 (አንድ መቶ ሺ ብር) በባንክ አሰርተው በአዋሽ ጉምሩክ ቅ/ፅ/ቤት ስም በማስያዝ በሲስተም አታች ማድረግ ይኖርባቸዋል።
4. የጨረታው መክፈቻ ሰዓት እና ቀንን ከኦክሽን ኢትዮጵያ ድህረ-ገፅ (Auction Ethiopia page) በማየት የጨረታው ሂደት ተጀምሮ ከማለቁ በፊት ዋጋ መስጠት ይችላሉ፡፡
5. ለጨረታው አሸናፊ ተጫራቾች ለጨረታው ዋስትና ያስያዙት (c.p.o) ከሚከፍሉት ዋጋ ጋር የሚታሰብላቸው ሲሆን ለተሸናፊ ተጫራቾች ደግሞ የጨረታ ውጤት ከተለጠፈበት ቀን ጀምሮ በ 3 የስራ ቀናት ውስጥ ተመላሽ ይደረግላቸዋል።
6. ከአሸናፊ ተጫራቾች ማሸነፋቸው በደብዳቤ ከተገለጸላቸው ቀን ጀምሮ በ3 ቀናት ውስጥ ያሸነፉበትን ገንዘብ ገቢ በማድረግ ዕቃውን በመረከብ ከመጋዝን ማውጣት ይኖርበታል፡፡
7. ከላይ በተ.ቁ.7 በተገለጹት ቀናት ውስጥ ክፍያውን ገቢ ያላደረጉ እና ንብረቱን ተረክበው ያልወሰዱ ተጫራቾች ለጨረታው ማሰከበሪያ ያሰያዙት ገንዘብ እና ለንብረቱ የከፈሉት ዋጋ ለኮሚሽኑ ገቢ ሆኖ ዕቃው በድጋሚ ለሸያጭ ይቀርባል፡፡
8. ቅ/ጽ/ቤቱ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
9. የኦክሽን ኢትዮጵያ auction Ethiopia መተግበሪያን በተመለከተ የጥሪ ማእከሉን ሰራተኛ ለማግኘት በስልክ ቁጥር 09-05-11-55-11/011-66-68-828 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡
10. ለተጨማሪ መረጃ ስልክ ቁጥር 09-13-07-40-27 ይደውሉ፡፡
የአዋሽ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት
