የአ/ከ/ክ/ከተማ ወረዳ 3 ጤና ጣቢያ ለ 2018 በጀት ዓ.ም የሚወገዱ ንብረቶችን በጨረታ ተጫራቾችን አወዳድሮ ንብረት ለማስወገድ ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የአ/ከ/ክ/ከተማ ወረዳ 3 ጤና ጣቢያ ለ 2018 በጀት ዓ.ም የሚወገዱ ንብረቶችን በጨረታ ተጫራቾችን አወዳድሮ ንብረት ለማስወገድ ይፈልጋል፤ በዚህ መሰረት
· ተጫራቾች የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ ሃምሳ ብር/ በመክፈል ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት አስር (10) ተከታታይ የስራ ቀናት ጤና ጣቢያው ቅጥር ግቢ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 407 የጨረታ ሰነዱን በመውሰድ የሚወዳደሩበትን የጨረታ ዋጋ ሰነዱ ውስጥ በሚገኝ የዋጋ ማቅረቢያ ዝርዝር መሰረት ሞልተው ያስገባሉ፡፡
· በ11ኛ ቀን 4፡00 ሠአት ተዘግቶ 4፡30 ሠአት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ጤና ጣቢያው የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል። በማንኛውም ምክንያት ዘግይቶ የቀረበ የጨረታ ሰነድ ወድቅ ይሆናል መ/ቤቱ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ጥብቅ ማሳሰቢያ∶- አሸናፊ ተጫራች ያሸነፈውን ንብረት በ3 ቀን ውስጥ ካላነሳ መ/ቤቱ ተጠያቂ አይሆንም።
አድራሻ፡- ከኮካ አደባባይ ወደ መሣለሚያ ወይም ከመሣለሚያ ወደኮካ አደባባይ በሚሄደው ዋና መንገድ ሲሄዱ የቀድሞ 24 ቀበሌ መዝናኛ ክበብ ፊት ለፊት ባለው ዳገታማ መንገድ 200 ሜትር እንደሄዱ በሚታየው ባለአራት ፎቅ ህንፃ ላይ ያገኙናል።
ለተጨማሪ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 0118-27-56-08 ወይም 0118-27-90-60
በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የወረዳ 03 ጤና ጣቢያ
