በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ፍ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት ከካፒታል በጀት ለመ/ቤቱ አገለግሎት የሚውሉ የቢሮ ፈርኒቸር እና ሞተር ብስክሌት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ፍ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት ከካፒታል በጀት ለመ/ቤቱ አገለግሎት የሚውሉ የቢሮ ፈርኒቸር እና ሞተር ብስክሌት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለዚህ በዚህ ጨረታ ለመሳተፍ የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች የሚከተለውን የመወዳደሪያ መስፈርት በማሟላት መወዳደር ይኖርባቸዋል፡-
1. በዘርፉ ህጋዊ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸውና የግብር ከፋይ መለያ /ቲን/ ቁጥር ያላቸው፣
2. የዘመኑን ግብር የከፈሉ መሆናቸውን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፣
3. ታክስ /ቫት ተመዝጋቢ የሆኑበትን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፣
4. ዝርዝር የጨረታ ሠነድ ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት በደቡብ ኢትዮጵያ ከልል መንግስት የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ፍ/ቤት የግዥ ክፍያ ንብረት አስ/ር ደጋፍ የሥራ ሂደት በመቅረብ የማይመለስ ብር 400 /አራት መቶ ብር/ ብቻ በመክፈል የጨረታ ሠነድ መግዛት ይኖርባቸዋል፣
5. በባንክ የተረጋገጠ 20,000 /ሃያ ሺህ ብር/ ብቻ የያዘ CPO ከሠነዱ ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል፣ ለጨረታው መወዳደሪያ የሚቀርብ CPO በባንክ ማህተምና በባንክ ኃላፊ ሠራተኞች ፊርማ የተረጋገጠ መሆን አለበት፣
6. ተጫራቾች የሚያቀርቧቸውን የዋጋ ማቅረቢያ ሠነዶቻቸውን ኦርጅናሉንና የኦርጅናል ኮፒ በፖስታ በማሸግ ሙሉ አድራሻቸውን በመጥቀስ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት እስከ መጨረሻው ቀን ከቀኑ 10፡00 ድረስ ለዚህ ጨረታ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ የጨረታ ሠነዶቻቸውን ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
7. ዝርዝር የጨረታ ሠነድ ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 /አሥራ አምስት ቀናት/ ከቀኑ 10፡00 ድረስ በሣጥኑ መጨመር ይኖርባቸዋል፡፡ በዕለቱ 10፡30 ታሽጎ በሚቀጥለው ቀን ማለትም በ16ኛው ቀን ከቀኑ 5፡30 ሕጋዊ ተጫራች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ የ16ኛው ቀን በዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው ስራ ቀን 5፡30 ሕጋዊ ተጫራች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ ካልተገኙም በኮሚቴው ይከፈታል።
8. ለጨረታው በዝርዝር ከተጠየቀው ዕቃ ዓይነት ውጪ ለመወዳደር ማቅረብ አይቻልም፣
9. በጨረታው ሠነድ የተፃፈውን የዕቃ ዓይነት ተጫራቾች በትከክል መሙላት አለባቸው፣ የሚያቀርቧቸው ዋጋ ከቫት ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል፣
10. ያሸነፈ ተጫራች ዕቃውን እስከ መ/ቤቱ ድረስ ማቅረብ ይኖርበታል፣ ፍርድ ቤቱ ለዚሁ ጨረታ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ፍ/ቤት
