የመተሐራ ስኳር ፋብሪካ ለሸንኮራ እርሻ የሚያገለግለውን ማሳ ምንጣሮ ለማሰራት ከዚህ በታች የተገለፀውን የዶዘር ኪራይ አገልግሎት ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ለሁለተኛ ጊዜ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር MSF/LP/01/2026
የመተሐራ ስኳር ፋብሪካ ለሸንኮራ እርሻ የሚያገለግለውን ማሳ ምንጣሮ ለማሰራት ከዚህ በታች የተገለፀውን የዶዘር ኪራይ አገልግሎት ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ጥቅል አንድ፣ ዶዘር ኪራይ (D7 Bulldozer/ Dozer) በድጋሚ የወጣ
በመሆኑም ከዚህ በታች የተጠቀሱትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾችን እንዲወዳደሩ ይጋብዛል።
1. ሕጋዊ የንግድ ሥራ ፈቃድ ያላቸው፣ የዘመኑን የሀገር ውስጥ ገቢ ግብር አጠናቀው የከፈሉና ለተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
2. በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው ድርጅቶች ለአንዱ ጥቅል የማይመለስ ብር 300 (ሶስት መቶ ብር) በመክፈል ዘወትር በሥራ ሠዓት ሜክሲኮ አደባባይ ፊሊፕስ ህንፃ ግዥ ቡድን 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 215 የተዘጋጀውን የጨረታ ሠነድ ገዝተው በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ፡፡
3. ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ ሲገዙ የንግድ ፈቃድ ይዘው መቅረብ ይኖርባችኋል፡፡
4. ተጫራቾች ከሚያቀርቡት ሠነድ ጋር የታደሰ የንግድ ፈቃድ የአቅራቢዎች የምዝገባ ሠርተፍኬት እና ለጨረታ ማስከበሪያ ብር 200,000.00 (ሁለት መቶ ሺህ) በሲ.ፒ.ኦ ማቅረብ አለባቸው።
5. ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዋጋ በራሳቸው የዋጋ ማቅረቢያ (Proforma invoice) ላይበማዘጋጀት በሰም በታሸገ ፖስታ በማድረግ እ.ኢ.አ. የካቲት 17 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ከጠዋቱ 4፡00 ሠዓት ድረስ ሜክሲኮ ፊሊፕስ ሕንጻ ቢሮ ቁጥር 19 ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
6. ጨረታው በዕለቱ የካቲት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:30 ሰዓት ላይ ከላይ በተጠቀሰው አድራሻ ቢሮ ቁጥር 19 ውስጥ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
7. ፋብሪካው ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ስልክ ቁጥር፡-0115-505607, 0115-505633
ሜክሲኮ አደባባይ ፊሊፕስ ሕንፃ
አዲስ አበባ
የመተሐራ ስኳር ፋብሪካ
