Tender Detail

Tender Details

  • Company በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ
  • Address ወልቂጤ ከተማ ፡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፡ ኢትዮጵያ, Phone: 011-3300112
  • Website
  • Deadline03 Mar 2026, 12:00 AM
  • magazineአዲስ ዘመን
  • Bid Document Price300.00
  • opening date2026-03-03 00:00:00
  • Categories Printing And Publishing , Educational And Training Equipment And Machinery

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ የተማሪ መማሪያ መጽሀፍ ህትመት ከቅድመ 1ኛ-8ኛ ክፍል መማሪያ መጽሀፍ በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።


የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 6/2018

 

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ የተማሪ መማሪያ መጽሀፍ ህትመት

1 ከቅድመ 1-8 ክፍል መማሪያ መጽሀፍ በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።

ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች በጨረታው መወዳደር ይችላሉ።

1.     በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፣

2.     የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፣

3.     የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN Number) ያላቸው፣

4.     የአቅራቢነት የምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ

5.     የግዢው መጠን ከብር 500,000 /አምስት መቶ ብር/ በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፣

6.     ተጫራቾች በጨረታው ለመሣተፍ ከላይ ከተራ ቁጥር 1 5 የተጠቀሰውንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፣

7.     ለሚወዳደሩባቸው ዕቃዎች ናሙና ሲጠየቅ ማቅረብ አለባቸው፣

8.     ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ብር 500,000 /አምስት መቶ ሺህ/ በባንክ በተመሰከረለት CPO ከቴክኒካል ኦርጅናል ዶክመንት ጋር አያይዘው በጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ስም ተዘጋጅቶ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።

9.     ተጫራቾች ከላይ የተጠቀሰውን የጨረታ ሰነድ ለመግዛት የምትፈልጉ የማይመለስ ብር 300 /ሶስት መቶ ብር/ በጉራጌ ዞን ገቢዎች መምሪያ በመክፈል ሰነዱን ከጉራጌ ዞን /መምሪያ ግዥ ንብ/አስ/የስራ ሂደት ሁለተኛ ፎቅ በመቅረብ መግዛት ይችላሉ፣

10. ማንኛውም ተጫራች ዕቃውን ጉራጌ ዞን /መምሪያ ወልቂጤ ከተማ ድረስ ለማቅረብ የሚያስችል ዋጋ የሚያሳይ የጨረታ ሰነድ ለቴክኒካል አንድ ኦሪጅናልና ሁለት ኮፒ እና ለፋይናንሻል አንድ ኦሪጅናልና ሁለት ኮፒ በማለት በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በጥንቃቄ ታሽጐ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 15 ተከታታይ ቀናት ጉራጌ ዞን /መምሪያ ግዥ ንብ/አስ/የሥራ ሂደት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ዘወትር በሥራ ሰዓት እስከ ቀኑ 1130 ሰዓት ድረስ ማስገባት አለባቸው።

11. ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት 16ኛው ቀን እስከ 600 ሰአት ድረስ የጨረታ ሰነድ ማስገባት ይችላሉ። ጨረታ የሚከፈትበት ቀን በዚሁ ቀን ከቀኑ 600 ሰዓት የጨረታ ሳጥኑ ታሽጐ በዚሁ ዕለት ከቀኑ 830 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ አዳራሽ በይፋ ይከፈታል። ጨረታው የሚከፈትበት ቀን በአል ወይም ቅዳሜና እሁድ ቀን ላይ ከዋለ ወደሚቀጥለው የስራ ቀን የሚሸጋገር መሆኑን እንገልጻለን።

12. /ቤቱ በጨረታው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

13. ለበለጠ መረጃ /ቤቱ ድረስ በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥር 011-3300112 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።

 

ማሳሰቢያ፡- የጨረታ ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ ለምታቀርቡ ተጫራቾች 90 ቀንና ከዚያ በላይ መሆን ይጠበቅበታል።

 

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ

Save Tender