የዘመን ኮንስትራከሽን ኮርፖሬሽን ውል ይዞ ለሚገናባው ለአዊ ብሄ/ዞን ከፍ/ፍ/ቤት ግንባታ ፕሮጀክት Supply and Fix Auditorium Chair & ashlary stone wall cladding to external wall surface አቅርቦትና ገጠማ ሥራ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት እና ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር 38/2018
የዘመን ኮንስትራከሽን ኮርፖሬሽን ውል ይዞ ለሚገናባው ለአዊ ብሄ/ዞን ከፍ/ፍ/ቤት ግንባታ ፕሮጀክት Supply and Fix Auditorium Chair & ashlary stone wall cladding to external wall surface አቅርቦትና ገጠማ ሥራ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት እና ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለዚህ በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች መሳተፍ የሚችሉ መሆኑን እየገለጽን፤
1. በዘርፉ ለዘመኑ የታደሰ የንግድ ሥራ ፈቃድና፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር (TIN) እና የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ የምስክር ወረቀት እና የንግድ ፈቃድ ለማደስ ግብር ስለመክፈላቸው የሚሰጥ ማስረጃ ያለው ያላት፣ በጨረታ ለመካፈል የሚያስችል ሰርተፍኬት ማቅርብ የሚችሉ፤ አቅርቦት እና ገጠማ ሥራ ከዚህ በፊት ለመስራታቸው ሕጋዊ ከሆነ ተቋም የመልካም ሥራ አፈጻጸም ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው።
2. የጨረታ ማስከበሪያ ቫትን ጨምሮ የጠቅላላ ዋጋውን 2% በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ (CPO) ወይም /unconditional bank guarantee/ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማስያዝ ይኖርበታል፡፡
3. የጨረታ ሰነዱ ባ/ዳር ከተማ ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ቀበሌ 11 እና አ/አበባ ለገሐር አመልድ ህንፃ 7ኛ ፎቅ በሚገኘው ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 02 የማይመለስ ብር 300 /ሶስት መቶ/ በመክፈል ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት መውሰድ ይችላሉ፡፡
4. የጨረታ መዝጊያ እና መክፈቻ ቀናት ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ኦርጅናልና ኮፒውን በመለየት በተለያዩ ፖስታዎች በጥንቃቄ በማሸግ ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15ኛው ቀን ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ድረስ ብቻ ባ/ዳር ዋናው መ/ቤት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ በእለቱ 8፡00 ሰዓት ሳጥኑ ታሽጎ 8፡30 ይከፈታል፡፡ 15ኛው ቀን የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን እስከ ቀኑ 8፡00 ሠዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ ጨረታው የሚከፈተው ባህር ዳር ዋናው ቢሮ አንደኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 108 የግን/ግብ/ግዥ እና አቅርቦት ኬዝ ቲም ቢሮ ክፍል ነው።
5. ውድድሩ በሎት /በጥቅል ዋጋ የሚታይ ይሆናል፣ ዝርዝር የጨረታ መመሪያው እና የውል ይዘቱ በጨረታ ሰነዱ ውስጥ የተገለፀ ስለሆነ ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በጥንቃቄ በማንበብ ዋጋቸውን በጨረታ መመሪያው መሰረት በሰነዱ ላይ ባለው የዋጋ ማቅረቢያ በመሙላት ማቅረብ አለባቸው።
6. ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በሕግ የተጠበቀ ነው።
ለማንኛውም ተጨማሪ ማብራሪያ ስልክ ባሕር ዳር 0582180538/09-18-01-06-17/09-13-27-60-57::
አዲስ አበባ:- 011-126-56-52/5145/0912085639
ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን
