ሞሐ የለስላሳ መጠጦች ኢንዱስትሪ ኃ/የተ/የግ ማህበር ሽሮ ሜዳ በሚገኘው የድርጅቱ መጋዘን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የተለያዩ ያገለገሉ ዕቃዎች በጨረታ በማወዳደር ባሉበት ሁኔታ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
ያገለገሉ ዕቃዎች የጨረታ ሰነድ የጨረታ
ቁጥር- Service 0004/2018
ሞሐ የለስላሳ መጠጦች ኢንዱስትሪ ኃ/የተ/የግ ማህበር ሽሮ ሜዳ በሚገኘው የድርጅቱ መጋዘን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የተለያዩ ያገለገሉ ዕቃዎች በጨረታ በማወዳደር ባሉበት ሁኔታ መሸጥ ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ ዕቃዎቹን መግዛት የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር) በመክፈል ለዚሁ የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ሸገር ዱቄትና ዳቦ ፋብሪካ ቅጥር ግቢ አዲስ በተገነባው ህንጻ ሦስተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 003 በመውሰድ በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ።
በዚሁ መሠረት፣
1. ተጫራቾች ለጨረታ የቀረቡትን የተለያዩ ዓይነት ያገለገሉ ዕቃዎችን ሽሮ ሜዳ በሚገኘው የድርጅቱ መጋዘን በአካል ተገኝተው በማየት ዋጋቸውን በታሸገ ኤንቬሎፕ ከየካቲት 26 ቀን 2018 ጀምሮ ለተከታታይ 15 የሥራ ቀናት እስከ ቀኑ 8:00 ሰዓት ድረስ ከላይ በተገለፀው መ/ቤት አድራሻ ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ።
2. ጨረታው በተመሳሳይ ቀን ከቀኑ 8፡00 ላይ ተዘግቶ 8፡30 ሰዓት ላይ በዋናው መ/ቤት መገኘት በሚፈልጉ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ፊት ይከፈታል።
3. በጨረታው የሚሳተፍ ተጫራች 20,000.00 (ሃያ ሺህ ብር) የጨረታ ማስከበሪያ CPO ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
4. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
አድራሻ፡-
አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ሸገር ዱቄትና ዳቦ ፋብሪካ ቅጥር ግቢ አዲስ በተገነባው ህንጻ 3ኛ ፎቅ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ መጋቢት 14 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ድረስ የጨረታ ሰነዱን በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማሸግና የጨረታ ሳጥን ውስጥ በማስገባት መወዳደር ይችላሉ፡፡
ማሳሰቢያ፣
- ሲፒአውን በማንኛውም ባንክ በሞሐ የለስላሳ መጠጦች ኢንዱስትሪ ኃ/የተ/የግ/ማህበር ስም ማሰራት ይችላሉ፡፡
- ዋጋ ሲያስቀምጡ ስርዝ ድልዝ ወይም በተሰጠው ሠንጠረዥ መሠረት በትክክልና በግልጽ የዋጋ ማቅረቢያ መሠረት ግልጽ መረጃ መስጠት ያለበት ሲሆን ነገር ግን የተሳሳተ ሰነድ ቢገኝ ውድቅ ይሆናል፡፡
ሞሐ የለስላሳ መጠጦች ኢንዱስትሪ ኃ/የተ/የግ/ማህበር
