የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በአዋጅ ቁጥር 97/90፣ 216/92 እና 1147/2011 መሠረት በብድር ዕዳ ምክንያት የተረከበውን ከዚህ በታች በሰንጠረዡ የተዘረዘረውን ንብረት በድርድር ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር 003/2018
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በአዋጅ ቁጥር 97/90፣ 216/92 እና 1147/2011 መሠረት በብድር ዕዳ ምክንያት የተረከበውን ከዚህ በታች በሰንጠረዡ የተዘረዘረውን ንብረት በድርድር ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
|
ተ.ቁ |
የተበዳሪው የመያዣ ሰጪው ስም |
የንብረት/ፕሮጀክት አድራሻ |
የንብረት/ ፕሮጀክት ዝርዝር |
የቦታ ስፋት (በሄክታር) |
የጨረታ መነሻ ዋጋ (በብር) |
የጨረታ ሁኔታ |
የጨረታ ደረጃ |
ጨረታው የሚካሄድበት ቀንና ሰዓት |
|
1 |
ኤም ዋይ ሹዝ ኤንድ ሌዘር ማኑፋክቸሪንግ ኃ/የተ/የግል/ማ |
አማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ደብረ ብርሃን ከተማ 09 ቀበሌ |
የጫማ እና የቆዳ ማምረቻ ፋብሪካ (በትግበራ ላይ ያለ) የሕንፃ ግንባታዎች፣ ማሸነሪዎች እና የኤሌክትሪክ ሥራዎች |
6.83 ሄክታር |
ብር 397,968,817.12 (ሦስት መቶ ዘጠና ሰባት ሚሊዩን ዘጠኝ መቶ ስልሳ ስምንት ሺህ ስምንት መቶ አስራ ሰባት ብር ከአስራ ሁለት ሳንቲም) |
ድርድር |
ሁለተኛ |
መጋቢት 21 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00-6፡00 ሰዓት |
|
2 |
ማጃንግ አግሮ ኢንዱስትሪ ኃ/የተ/የግል ማህበር |
ጋምቤላ ህ/ብ/ክ/መ፡ ማጃንግ ዞን፣ መንገሺ ወረዳ፣ አሽኔና ባያ ቀበሌ |
የመስኖ እርሻ እና ግንባታዎች፣ የእርሻ ማሽነሪዎች፣ ተሽከርካሪዎች፣ 145 ሄክታር ላይ የተተከለ የሙዝ ቋሚ ተክል ያለው |
1000 ሄክታር በሊዝ የተገኘ መሬት |
375,513,976.00 (ሶስት መቶ ሰባ አምስት ሚሊዮን አምስት መቶ አስራ ሶስት ሺህ ዘጠኝ መቶ ሰባ ስድስት ብር) |
ድርድር |
ሁለተኛ |
መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00-6፡00 ሰዓት |
ማሳሰቢያ፡-
1. ተጫራቾች የማይመለስ ብር 100 /አንድ መቶ ብር/ በመክፈል የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ በመግዛት ንብረቶቹን የሚገዙበትን ዋጋ፣ ስምና አድራሻቸውን በፎርማቱ ላይ በመጥቀስ በባንኩ ዋና መ/ቤት ሁለተኛ ታወር ምድር ቤት ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሣጥን ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣ ከሦስተኛው ቀን ጀምሮ ለኤም ዋይ ሹዝ ኤንድ ሌዜር ፋብሪካ እስከ መጋቢት 21 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡50 ሰዓት፣ እና ለማጃንግ አግሮ ኢንዱሰትሪ እስከ መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም ሆኖ ለሁሉም ከጠዋቱ 3፡50 ሰዓት ድረስ በማስገባት፤ ከቀኑ ከ4፡00-6፡00 ባለው ጊዜ ውስጥ ቀርበው መደራደር ይችላሉ፡፡
2. ተጫራቾች የጨረታውን መነሻ ዋጋ 10 በመቶ በባንክ ክፍያ ማዘዣ /ሲ.ፒ.ኦ/ ብቻ በማስያዝ መጫረት ይችላሉ፡፡
3. አሸናፊ የሆነው ተጫራች ያሸነፈበትን ቀሪ ገንዘብ በ15 /በአስራ አምስት/ ተከታታይ ቀናት ውስጥ አጠቃሎ መክፈል ይኖርበታል፤ በዚህ ጊዜ ውስጥ ካልከፈለ ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ሆኖ ጨረታው ይሰረዛል፡፡
4. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በሰንጠረዡ በተመለከተው ቀንና ሰዓት በባንኩ ዋናው መ/ቤት ታወር ሁለት 5ኛ ፎቅ በሚገኘው መሰብሰቢያ አዳራሽ ይካሄዳል፡፡ ሕጋዊ ሰውነት ያላቸው አካላትን ወክሎ በጨረታው ለመሳተፍ የሚቀርብ ሰው የማህበሩ መመስረቻ ጽሑፍ/መተዳደሪያ ደንብ ከእነ ማሻሻያዎቹ (ካለ)፣ የንግድ ምዝገባ፣ የንግድ ፍቃድ፣ ሌሎች አስፈላጊ ማስረጃዎችን እና የተረጋገጠ የውክልና ሥልጣን ሰነዶችን ይዞ መቅረብ ይኖርበታል፡፡
5. 15% የተጨማሪ እሴት ታክስና ሌሎች ገዢ እንዲከፍላቸው በሕግ የተወሰኑ ክፍያዎችን፣ የስም ማዛወሪያ ክፍያን ጨምሮ ገዢው ይከፍላል፡፡
6. አንዳንድ የድርጅቱ ንብረቶች የጉምሩክ ቀረጥና ታክስ ያልተከፈለባቸው ስለሆኑ ገዢው የቀረጥ ነጻ መብት ሊኖረው አሊያም የሚፈለገውን ቀረጥ/ታክስ ለመንግሥት ለመክፈል ይገደዳል፡፡
7. የማጃንግ አግሮ ኢንዱስትሪ ኃ/የተ/የግ/ማህበር የሥራ እንቅስቃሴ ያልተቋረጠ በመሆኑ እሸናፊው ከግዢው ዋጋ በተጨማሪ ያልተሰበሰበ ወይም በክምችት ላይ ያለ የሙዝ ምርት በርክክብ ወቅት በሚደረስበት የትመና ዋጋ መሠረት በጥሬ ገንዘብ መግዛት ይችላል፡፡
8. ተጫራቾች ንብረቱን ለመጎብኘት ከፈለጉ አስቀድሞ ከባንኩ ጋር ቀጠሮ በመያዝ ከጨረታው ቀን በፊት መነብኘት ይችላሉ፡፡
9. ባንኩ ለሽያጭ የቀረቡትን ንብረቶች የሚሸጠው ከተቻለ ሙሉ በሙሉ በጥሬ ገንዘብ ሲሆን አሸናፊው በባንከ ብድር ፖሊስ መሠረት አስፈላጊውን መስፈርቶች ካሟላና ፕሮጀክቱን የሚያስቀጥል ከሆነ ንብረቱን በከፊል ብድር ለመግዛት መጠየቅ ይችላል፡፡
10. የጨረታ አሸናፊው የማጃንግ አግሮ ኢንዱስትሪ ኃ/የተ/የግ/ማህበርን ቋሚ ሠራተኞች በሙሉ ከመብትና ጥቅማቸው ጋር መረከብ ይጠበቅበታል፡፡
11. የንብረቱ ስመ-ንብረት ለገዥው እንዲዞር ባንኩ ለሚመለከተው መንግሥታዊ አካል ደብዳቤ ይፅፋል። ገዥው ጉዳዩን ተከታትሎ ያስፈፅማል።
12. በጨረታው ላይ መገኘት የሚችሉት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው ብቻ ናቸው።
13. በጨረታው ዝርዝር እና ተጨማሪ መረጃን ለማግኘት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ዋና መ/ቤት ታወር ሁለት ሦስተኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው የኦንጎይንግ ኮንሰርን ፕሮጀክትስ እና አኳየርድ አሴትስ ማኔጅመንት ዳይሬክቶሬት በአካል በመቅረብ ወይም በስልከ ቁጥር 011-524-53-73/ 011-524-42-69 ደውሎ ማግኘት ይቻላል፡፡ የመያዣ ንብረቶቹን መጎብኘት የሚፈልግ ከዳይሬክቶሬቱ ጋር አስቀድሞ ቀጠሮ በመያዝ መጎብኘት ይቻላል።
14. ባንኩ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
